የVOA ጋዜጠኞች ቅሌት ዛሬም ቀጥሏል
VOA ማክሰኞ በቦታው ተገኘሁ ብሎ የሰልፈኞቹን ብዛት በተዛባ ሁነታና በቅጥፈት 15ና 20 ናቸው ብሎ ተናግሮ ሲያበቃ፤ ዛሬም ወያኔን ለመጥቀም መረጃ ማዛባቱን ቀጥሎበት ለአድማጭ ያልተረጋገጠ፣ ለማያውቁ የዋሆች ክርክር ውስጥ የሚያስገባና፣ የበረራ ቲኬት ተገዝቶላቸው በመከራ ከየ እስቴቱ መጥተው በመዋጮ የተሰባሰቡትን ሆዳሞች ተጨምረውበት እንኳን እጅግ አናሳ የነበሩትን የወያኔ ደጋፊዎችን በማምታታት አብዝቶ ለማሳየት፤ ከጋዜጠኛ የማይጠበቅ እጅግ የወረደ ዘገባ አቅርቧል።
እንደው እስኪ ፍረዱ ሰልፉ ከተጠናቀቀ ከ24 ሰአታት በላይ ካለፉ በሗላ ጠይቆ የተሰላፊዎቹን ተወካዮች ለአድማጭ አሃዞችን እንደ እውነት ማቅረብ ምን ይባላል!? ወያኔ ተዋሸለትም፣ ተደበቀለትም፤ ከህዝብ ትከሻ ላይ አሽቀንጥረን የምንጥልበት ጊዜው በጣም ቀርቧል። ለነገሩ ለተከፈለው ገንዘብ ብሎ የተጠራቀመ፤ የገዛ ባንዲራውን እንኳን የማይለይ ሆዳም ቢሰባሰብ ምን ይፈይዳል!? “ሺሺሺ… አንድ ጎማ አይነፋም” ይሉ የለ… !
No comments:
Post a Comment