Tuesday, 9 December 2014

በሰላማዊ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ጥቃት እናወግዛለን !!!
በአብዛኛው በወጣት ወንዶችና ሴቶች የተገነባው ሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነበት የዘጠኝ ፓርቲዎች ኅበረት፣ “ነፃነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የተሰኘ የአንድ ወር መርሀ ግብር አውጥቶ፤ ችግሮችን ተጋፍጦ አብዛኛውን ተግባራዊ አድርጓል። የመርሀ ግብሩ አቢይ አካል የነበረውና በህዳር 27 እና 28 ሊከናወን ታድቆ የነበረው የ24 ሰዓት የአደባባይ ተቃውሞ ግን በአገዛዙ የኃይል እርምጃ ምክንያት በታቀደው መንገድ ሊከናውን አልቻለም። የህወሓት ቅልብ የሆኑት ሲቪል የለበሱ ሰላዮችና የፌደራል ፓሊስ በተቃውሞው ተሳታፊዎች ላይ ኢሰብዓዊ የሆነ ጥቃት ፈጽመዋል።
ከጅምሩ፣ የፓርቲዎቹ ኅበረት የተቃውሞ ማሳወቂያ ደብዳቤውን ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለማስገባት የገጠመው ችግር የህወሓት አገዛዝ የመንግሥትን መዋቅር ለፓ...ርቲ ሥራ፤ የመንግሥት ተቀጣሪዎችን ደግሞ እንደ ህወሓት አገልጋዮች የሚጠቀምባቸው መሆኑ አንዱ ማሳያ ሆኗል። ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ማሳወቅ የፈለጉት ፓርቲዎች ህወሓት የዘረጋውን አፋኝ ሥርዓት የሚታገሉ በመሆናቸው ብቻ ደብዳቤዓቸውን የሚቀበል እንኳን አጥተው ተጉላልተዋል። ለሰልፉ ቅስቀሳ ማድረግም በራሱ እንደ ወንጀል ተቆጥሮ ወጣቶች ተንገላተዋል፣ ተደብድበዋል፣ ታስረዋል። ያም ሆኖ ውጣ ውረዶች ታልፈው ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ. ም. ደረሰ።
የኅበረቱ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ጥሪውን የሰማ ሕዝብ ወደ መስቀል አደባባይ ማምራት ሲጀምር ሲቪል የለበሱ የአገዛዙ ታጣቂዎች እና ፌደራል ፓሊሶች ከሰንደቅ ዓላማዎችና መፈክሮች ባለፈ አንዳች ነገር ያልያዙትን እድሜያቸው ከሃያዎች ያልዘለሉ ውድ የኢትዮጵያ ልጆችን ደብድበዋል፤ ብዙዎቹም አፍነው በአሰቃቂ ሁኔታ እያንገላቱ ወደ እስር ቤቶች ወስደዋል። ወጣቶች ተወልደው ባደጉበት አገር፤ ስሜታቸውን በነፃነት ለመግለጽ በመድፈራቸው ብቻ በጭካኔ ተረግጠዋል፤ ተፈንክተዋል፤ እጅና እግሮቻቸው ተሰብሯል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ይህ የህወሓትን ፋሺስታዊ እርምጃ አጥብቆ ይቃወማል። ግንቦት 7፣ ህወሓት ከስልጣን እስካልተወገደ ድረስ እንዲህ ዓይነቱን ፋሺስታዊ ተግባር መፈፀሙን የማይተው እኩይ ኃይል እንደሆነ ያውቃል፤ በዚህም ምክንያት የትግላችን ግብ ህወሓትን ማስወገድና በምትኩ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መመሥረት መሆን ይኖርበታል ብሎ ያምናል፤ ለዚህም ይታገላል።
ግንቦት 7፣ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ.ም. “መብቶቻችንን በህወሓት ዘረኛ አምባገነኖች አናስነጥቅም” በማለት አደባባይ የወጡ ወጣቶችን ጽናት ያደንቃል። ህወሓት የሚለውን ሳይሆን የይስሙላ ህጉ የፈቀደላቸውን ለማድረግ በመድፈራቸው በህወሓት የህግ ማዕቀፍ ውስጥ ሆኖ የሚደረገውን ትግል አንድ እርምጃ ወደፊት አራምደውታል።
እያንዳንዱ የፓለቲካ ድርጅት ከዚህ ኩነት የሚወስዳቸው ተጨማሪ ትምህርቶች ቢኖሩም የሚከተሉትን ነጥቦች ብዙዎችን ያስማማሉ ብለን እናምናለን።
1. ህወሓት በምንም ዓይነት ቢሆን የያዘውን ስልጣን ለሕዝብ ፈቃድ ማስገዛት አይፈልግም፤
2. ህወሓት አገራችን ወደ ትርምስ እየገፋት እንደሆነ ግልጽ እየሆነ መጥቷል፤
3. ስልጣኑን የሚያሳጣው ከመሰለው እና አቅሙ እስካለው ድረስ ዘግናኝ እርምጃዎችን ከመውሰድ አይመለስም፤
ከህወሓት አገዛዝ መገላገል የሚቻለው ተገዶ ሲወገድ ብቻ ነው። ህወሓት እንዲወገድ ደግሞ የመጨቆኛ አቅሙ መዳከም ይኖርበታል። ህወሓትን የማስወገጃ አማራጭ መንገዶች ብዙ ሲሆኑ ተቀናጅተው ቢሠሩ የበለጠ ውጤታማ ይሆናሉ ብለን እናምናለን፤ “ሁለገብ ትግል” የምንለው የትግል ስልት ጭብጥ ይህ ነው። “እምቢ ለነፃነቴ” ብሎ የተነሳ ሕዝብ ህወሓትን ምን ያህል እንደሚያስደነግጥ በተደጋጋሚ ታይቷል። ህዳር 27ን መንደርደሪያ አድርገን በመውሰድ ከዚህ በተሻለ ለተደራጀ ሕዝባዊ እምቢተኝነትና አመጽ ራሳችን እናዘጋጅ።
በዚህ አጋጣሚ ግንቦት 7፣ ለመከላከያ ሠራዊት እና ፓሊስ አባላት ተደጋጋሚ ጥሪዎችን ማድረግ ይሻል። የመከላከያ ሠራዊት እና ፓሊስ አባላት እንደማንኛውም የኢትዮጵያ ዜጋ በህወሓት ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ የተበደላችሁ መሆኑን እናውቃለን። የህወሓት ሹማምንት ከሆኑ አዛዦቻችሁ መላቀቅና ራሳችሁን ነፃ የማውጣት ኃላፊነት የወደቀው በእናንተው በራሳችሁ ላይ ነው። ሠራዊቱ ራሱን በራሱ ነፃ ማውጣት ይኖርበታል። የጊዜ ጉዳይ ካልሆነ በስተቀር ህወሓት መወገዱ የማይቀር በመሆኑ ሠራዊቱ ራሱን ነፃ አውጥቶ ከሕዝብ ጋር ካልወገደ እጣ ፈንታው የተሸነፈ ሠራዊት መሆን ነው። ከዚህ በላይ የሠራዊቱ አባል እየደበደበ ያለው የራሱን ልጅ፣ ወንድሙን ወይም እህቱን እንደሆነ ይወቅ። ይህ ወሳኝ ጊዜ ነው እያንዳንዱ የሠራዊቱ አባል በግል ኃላፊነት ያለበት መሆኑ ሊሰማው ይገባል።
በሁሉም ዓይነት የትግል ዘርፎች የኢትዮጵያ ወጣቶች በስፋት እየተቀላቀሉ መሆኑ ተስፋ ሰጪ ነው። ጊዜው የለውጥ ነው። የተለያዩ ስትራቴጂዎች ተደጋግፈው እንዲሄዱ መደረግ ያለበት ወቅት ላይ ነን። በህዳር 27 ቀን በህወሓት ቅልብ ሰላዮችና የፌደራል ፓሊሶች አማካይነት የደረሰው ጉዳትና የፈሰሰው ደም ለፍትህና ለነፃነት የተከፈለ ዋጋ ነው። ህመማችሁ ህመማችን፤ ትግላችሁ ትግላችን ነው። የተለያዩ መንገዶች ወደ ነፃነት አደባባይ እያመሩ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

Monday, 8 December 2014

መሪዎች ቢታሰሩም ትግሉ እንደማይቆም የ 9 ፓርቲዎች ትብብር አመራሮች አስታወቁ

-የምርጫ ስርዓት ለውጥ እንዲደረግ ለመጠየቅ ህዳር 27 ቀን የአዳር ተቃውሞ ሰልፍ ለማድረግ ወደ አደባባይ በወጡት 9 የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች ላይ የፌደራል ፖሊስ አባላት ድብደባ በመፈጸም ወደ እስር ቤት ቢወስዱዋቸውም፣ የትብብሩ አመራሮች ግን ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልና ኢትዮጵያውያን ለትግሉ የሚያደርጉትን አስተዋጽኦ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጠይቀዋል።
ሶስተኛ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት ውስጥ ታስረው የሚገኙት የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት፣  አቶ ኤርጫፎ ኤርዳሎ፣ አለሳ መንገሻና ሌሎችም አመራሮች አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ፣ በጨርቆስ ታስረው የሚገኙት እነ አቶ ግርማ በቀለ ደግሞ የ7 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል።
አመራሮቹ ሀግመንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል ለመናድና የተከለከለ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ወንጀል መከሰሳቸውን ታውቋል።
በፍርድ ቤት አካባቢ ሆነው ጉዳዩን ከተከታተሉት መካከል ናትናኤል ያለምዘውድ ለኢሳት ሲናገር፣ አብዛኞቹ አመራሮች ሲሄዱ ያነክሱ እንደነበር ገልጾ፣ ኢ/ር ይልቃል እጁ አካባቢ መመታቱን፣ ብርሃኑ ተክለያሬድ ደግሞ እጅና እግሩ አካባቢ በጨርቅ ተጠቅሎ ማየቱን ገልጿል። ሴት እስረኞችም ሲጓዙ ያነክሱ እንደነበር በተለይ አንደኛዋ ኩላሊቷ አካባቢ መመታቱዋን እንደገለጸችለት ተናግሯል ሴት እስረኞችን ለመጠየቅ በሄደበት ወቅት ለአጭር ደቂቃዎች ራቅ ብሎ ለማናገር መቻሉን የገለጸው ዮሴፍ ተሻገር በበኩሉ፣ ሴቶች በጠንካራ መንፈስ ላይ እንደሚገኙ ገልጿል።
ኮተቤ አካባቢ ታስረው ስለሚገኙት የድርጅት መሪዎችና አባላት ጉዳይ በስፍራው በመገኘት ለመታዘብ የቻለው አቶ እምላሉ ፍሰሃ እንደገለጸው ደግሞ ምንም እንኳ እስረኞቹ መጸዳጃ ቤት አካባቢ በመታሰራቸው እንዲሰቃዩ ቢደርግም አሁንም በጠንካራ መንፈስ ላይ መሆናቸውን ገልጿል።
መንግስት የወሰደው እርምጃ በትብብሩ የወደፊት የትግል አካሄድ ላይ ተጽአኖ ይኖረው እንደሆን የተጠየቁት የመኢዴፓ ሊቀመንበርና የትብብሩ ገንዘብ ያዥ አቶ ኑሪ ሙዲሰር ሲመልሱ ” መንግስት እስረኞች ይፈቱ አይፈቱ ወደ ሚል አታካራ እንድንገባ ቢፈልግም፣ እኛ ግን ትግሉን ወደ ፊት ከመግፋት ውጭ ሌላ አማራጭ የለንም” ብለዋል።
ኢትዮጵያውያን በሙሉ ለትግሉ አስፈላጊውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉም አቶ ኑሪ ጠይቀዋል።
በሌላ በኩል ደግሞ አንድነት ፓርቲ በ9 ፓርቲዎች ላይ የተወሰደውን እርምጃ አውግዟል። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ  ” የዘጠኙ ፓርቲዎች አመራሮችና አባላት በህገ መንግስቱ ላይ የተቀመጠውን ሰላማዊ ሰልፍ የማድርግ መብት ከመጠቀም ውጪ ያጠፉት ምንም ዓይነት ነገር ስለሌለ በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል።” ብሎአል።  ፓርቲው ” የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ህዝብ ይህ ህገወጥና አረመኔያዊ ድርጊት በዝምታ ሊያልፈው አይገባም፤ ኢህአዴግን በቃህ ሊለው ይግባል።” በማለት በመግለጫው አስታውሷል።

እነ ግርማ በቀለና ጌታነህ ባልቻ መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውድመዋል ተብለው ተከሰሱ

እነ ግርማ በቀለና ጌታነህ ባልቻ መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውድመዋል ተብለው ተከሰሱ
ለአዳር ሰላማዊ ሰልፉ መስቀል አደባባይ ተይዘው ጨርቆስ ፖፖላሬ ታስረው የሚገኙት የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፀኃፊ አቶ ግርማ በቀለ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የጥናትና እስትራቴጅ ክፍል ኃላፊ ጌታነህ ባልቻን ጨምሮ 27 ያህል የትብብሩ አመራሮች፣ አባላትና የሰልፉ ተሳታፊዎች ዛሬ ህዳር 29/2007 ዓ.ም ጨርቆስ አካባቢ የሚገኝ ፍርድ ቤት ቀርበው ‹‹መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውድመዋል፡፡›› በሚል ተከሰዋል፡፡
ፖሊስ ‹‹ታሳሪዎቹ መስቀል አደባባይ ላይ ንብረት አውድመዋል፣ የጠፉ ንብረቶችና ያልተያዙ ግብረአበሮቻቻው ስላሉ ለምርመራ 14 ቀን ይሰጠኝ›› ሲል ጠይቋል፡፡ ታሳሪዎቹ በበኩላቸው ‹‹እኛ መስቀል አደባባይ ላይ ምንም አይነት እንቅስቃሴ ሳንጀምር ነው የታሰርነው፣ ምንም ...ያወደምነውም ሆነ የወሰድነው ንብረት የለም፡፡›› ሲሉ የፖሊስን ክስ አጣጥለዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በህጋዊ መንገድ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ በሚዘጋጁበት ወቅት መያዛቸውን በመግለጽ የዋስትና መብታቸው ተጠብቆ እንዲለቀቁ ጠይቀዋል፡፡ ሆኖም ዳኛው የ7 ቀን ቀጠሮ አስተላልፈውባቸዋል፡፡
በተመሳሳይ በዛሬው ዕለት አራዳ ምድብ ችሎት ቀርበው የ14 ቀን ቀነ ቀጠሮ የተሰጠባቸውና በሶስተኛ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙት ታሳሪዎች በደረሰባቸው ድብደባ ምክንያት ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል፡፡ ወደ ሆስፒታል ከተወሰዱት መካከል ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፣ እየሩስ ተስፋው፣ ጋዜጠናኛ በላይ፣ አቤል ኤፍሬም፣ ብርሃኑ ተክለያሬድ፣ ስሟ ያልተጠቀሰች አንዲት ሴትና ሌሎች በርካታ ወንዶች እንደሚገኙበት ታውቋል፡፡ ሶስተኛ ከሚገኙት ታሳሪዎች መካከል ከሴቶቹ ንግስት ወንዲፍራውና ምኞቴ መኮንን ከፍተኛ ድብደባ እንደደረሰባቸው እና አብዛኛዎቹ ወንዶች ለየብቻቸው ጨለማና ቀዝቃዛ ቤት ውስጥ እንደታሰሩ ተገልጾአል፡፡

70 ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር ላይ ሰጥመው መሞታቸውን የየመን ባለስልጣናት ገልጸዋል

ስደትን የህይወታቸው የመጨረሻ አማራጭ በማድረግ በጅቡቲ በኩል አድርገው ወደ የመን ለመግባት የሞከሩ 70 ኢትዮጵያውያን ቀይ ባህር ላይ ሰጥመው መሞታቸውን የየመን ባለስልጣናት ገልጸዋል።
ታይዝ በምትባለዋ ግዛት የሚገኙ ባለስልጣናት ለአሶሴትድ ፕሬስ እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያውያኑን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረችው ጀልባ ባጋጠማት ከባድ አውሎ ንፋስና ማእበል አል ማክታ እየተባለ ከሚጠራው ወደብ ራቅ ብሎ ለመስመጥ ተገዳለች። ባለስልጣናቱ እንዳሉት ጀልባዋ 70 ኢትዮጵያውያንን ጭና የነበረ ሲሆን በደጋው ሁሉም ኢትዮጵያውያን አልቀዋል።
የመን የሚገኘው ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት በበኩሉ በጀልባዋ ላይ የነበሩት 81 ሰዎች ሲሆኑ፣ 71 ኢትዮጵያውያንና 9 ሶማሊያዎች አልቀዋል። አይ ኦ ኤም የተባለው የስደተኞች ድርጅት አስከሬን ለመሰብሰብ ሙከራ ቢደረግም እስካሁን ምን ያክል አስከሬን እንደተሰበሰበ ለማወቅ አለመቻሉን ገልጿል....

Wednesday, 26 November 2014


የታሰሩ ዜጎች አሸባሪዎች ስለነበሩ አልነበረም፡፡የፖለቲካ ጨዋታው ሌላ በመሆኑ ምክንያት የዚህን ሁሉ ህዝብና ባለሙያ ጩኽት ኢህአዴግ ከምንም ሳይቆጥር የዚህን አዋጅ ወደ ሚሞግቱት ፊቱን በማዞር ሲቃወሙ የነበሩ ግለሰቦችንና ተቋማት ላይ በጠራራ ጸሀይ የወሰደው እርምጃ በእርግጥም ትክክል እንደነበሩ አረጋግጧል፡፡የፀረሽብር አዋጁ በፀደቀ ማግስት የያኔው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ የመንግስታቸውን ሪፖርት ለማቅረብ ፓርላማ ተገኝተው ስለአዋጁ ካብራሩ በኋላ ከምክር ቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስን ሰጥተው እብዳጠናቀቁ ለአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ‹‹ዋ ዋጋ ትከፍላላችሁ በማለት በፓርቲው አመራርና አባላት ላይ ሽብር አወጁ ››ያኔ ይህንን ማስፈራሪያቸውን በቃላት ብቻ ገድበውት አላለፉም፡፡አንዴ ሰይፋቸውን መዘዋልና ፓርተአቸው አስቀድሞ ጣት የቀሰረባቸውን እስር ቂምና ቁርሾ የተያዘባቸው በርካታ ትንታግ ፖለቲከኞችን፤ጋዜጠኞችን ለሀገራቸው ተስፋን የሰነቁ ኮኮብ ልጆችን በአዋጁ ጎራዴ ሰየፉት ፡፡ከእነዚህ ሰለባዎች ውስጥ በትህትናው ፡በፀባዩና በምግባሩ እንዲሁም በአካዳሚክ እውቀቱ የሚታወቀው ወጣቱ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አንዷለም አራጌ ፤የአንድነት ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል ወጣቱ ፖለቲከኛ ናትናኤል መኮንን፤መምህር አሳምነው ብርሀኑ፤አንጋፋው የፕሬስ ተሟጋችና አለማቀፍ የፖለቲካ ተንታኝ ጎልማሳው እስክንድር ነጋ ፤የኦፌዴን ምክትል ለቀመንበርና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር በቀለ ገርና የኦህኮ አመራር አባል የነበሩት አቶ ኦልባና ሌሊሳን እነደምሳሌ መጥቀስ የሚቻሉ የፀረሽብር አዋጁ ሰለባዎች ናቸው፡፡

Tuesday, 18 November 2014

ታሪካችን የደብተራ ነው አላችሁኝ?
በፋሲል የኔያለም (የኢሳት ጋዜጠኛ)
ከዋልን ካደርን ገና ብዙ ጉድ እንሰማለን። የኢትዮጵያን ታሪክ ማጠልሸት ሰሞኑን እንደ ወረርሽኝ ሆኗል። የኢትጵያን ታሪክ የደብተራ ተረት ነው ብሎ ማጣጣል፣ ደብተራን ከአማራ ጋር ብቻ ማያያዝ ያለማወቅ በሽታ ካልሆነ ምን ይባላል? አለማወቅን ማወቅ ጤና፣ አለማወቅን አለማወቅ ደግሞ በሽታ ነው።
...
ደብተራ ያየውን የሰማውን በከተበ ለምን ይንቋሸሻል? የደብተራ ጥፋቱ አስቀድሞ መሰለጠኑ ነው፤ ፊደል የስልጣኔ በር ነው፤ ደብተራ ደግሞ ፊደል የቆጠረ የመጀመሪያ ሰው ነው፤ የኢትዮጵያ ደብተሮች በጊዜያቸው ከነበሩት ሰዎች አስቀድመው የሰለጠኑ ናቸው፤ ስልጣኔውን ያገኙትም በፊደል በኩል ነው። አስቀድመው በመሰልጠናቸውም፣ ለሁላችንም የሚሆን ነገር ጽፈው አለፉ። ባይሰለጥኑ ኖሮ ታሪክን ለመጪው ትውልድ ስለማስተላለፍ አይጨነቁም ነበር። ከደብተራ ውጭ ታሪክን ለመጪው ትውልድ ጽፎ ስለማስቀረት ያሰበ ማን ነው? ተራው ገበሬ ዝናብ መጣ ሄደ፣ ተራው ነጋዴ አሞሌ ተወደደ ረከሰ፣ ተራው ወታደር ድንበር ሰፋ ጠበበ፣ ንጉስ ግብር ጨመረ ቀነሰ ከማለት ውጭ ታሪክ ጽፎ ስለማስተላለፍ ተጨንቆ ያውቃል? ስለጥበብ ስለውበት ተጨንቆ የጻፈውም ደብተራው ነው።
ደብተራ ባየው በሰማው፣ የጆግራፊ እውቀቱ፣ የእግሩ ጥንካሬ፣ የቀለም አቀባበሉና እድሜው በፈቀደለት መጠን ጻፈ። ሲጽፍ ይጨምራል፣ ይቀንሳል። የጨመረውን የቀነሰውን ማስተካከል ከደብተራ የተሻለ እውቀት ያገኘው የሁዋለኛው ትውልድ ሃላፊነት ነው። ታዲያ እንዲህ ሲባል ደብተራን በማድነቅ እንጅ በማንቋሸሽ አይጀመርም። ኒውተን ጋሊሊዮን አንቋሾ ጥናት አልጀመረም፣ አንስታይን ኒውተንን አንቋሾ አልተነሳም። የኛ ዘመንኛ ጻፊዎች ደግሞ የሁዋላውን አንቋሾ መጀመር እውቀት ይመስላቸዋል። ጽሁፋቸውም በውሃ ላይ እንደበቀለ ተክል የሚሆነው ለዚህ ነው፣ ስር አልባ ነው፤ እፍ ቢሉት እንደ ላባ በኖ ይጠፋል።
አሁን ደብተራ ባይጽፍ ኖሮ ታሪካችን የሰሃራ በታች ካሉት አገራት ይለይ ነበር?። ከሰራሃ በታች ካሉ አገራት በራሱ ቋንቋ ታሪኩን ጽፎ ያስቀረ ከእኛዋ ኢትዮጵያ ውጭ ሌላ አለ? አብዛኛው የጥቁሩ የአፍሪካ ታሪክ የተጻፈው በቅኝ ግዛት ጊዜ አይደለምን? ፈረንጆቹ ለእነሱ በሚጥማቸው መንገድ አይደለም የከተቡት? ምንጫቸውስ ምንድነው? ህንጻዎች እና ቁሳቁሶች አይደሉም? ታዲያ ደብተራ ታሪክ ጽፎ ባስቀረ፣ ድንጋይና ቁሳቁስ ከመፈለግ ባዳነ ለምን ይሰደብ?
ደብተራ ታሪክ የሚጽፈውስ በእኛ አገር ብቻ ነው? የአውሮፓ የጥንት ታሪክ በማን ተጻፈና ነው? የአውሮፓ የታሪክ ወመዘክር ካቶሊክ ቤ/ክ አይደለችም? ስኮላስቲስዝም የሚባለው ታላላቅ ምሁራን የወጡበት የትምህርት ስርዓት የሚመራው በደብተሮች አልነበረምን? የአውሮፓን ታሪክ ከደብተራ ታሪክ መነጠል ይቻላል? የፈረንጅን ደብተራ አቆለጳጵሰን የሃበሻን ደብተራ የምናዋርድበት ምክንያቱ ምን ይሆን? አውሮፓ ውስጥ በኢራስመስ ስም ስኮላርሽፕ የምትመጣው ኢራስመስ ማን ሆነና ነው? የፈረንጅ ደብተራ አይደለም?
ከአገራችን ደብተራ ብንማር ኖሮ ዛሬ እንደ አውሮፓውያን 6 ቢሊዮን ኪሜትር የሚጓዝ መንኮራኩር እናመጥቅ ነበር። ኮፐርኪነከስና ጋሊሊዮ ማን ናቸው? ደብተሮች አይደሉም? የሰማይን ምስጢር ለማወቅ ሰማይ ሲያንጋጥጡ በመኖራቸው የኸው ለዛሬው አስደማሚ የህዋ ምርምር በር ከፈቱ። የእኛዎቹ ደብተሮች ስለአስትሮሎጂ ምርጥ የሆነ እውቀት ቢያከማቹም አጣጥለነው በዘመናዊ መንገድ ሳንማረው ቀረን፤ የማጣጣላችን ውጤትም ፈረንጅ ወደ ላይ ሲመጥቅ እኛ መሬት መሬት እያየን ተቀብረን ቀረን። ዛሬ በየጋዜጣው ጀርባ የምታነበው ሆሮስኮፕ፣ የእኛ ደብተሮች ከዘመናት በፊት ኮከብ ቆጠራ እያሉ ሲያሰሉት የነበረ ነው። ፈርንጅ የተለየ ስም ስለሰጠው እንጅ ስራውና ይዘቱ ያው ነው። ልጅ እያለሁ አንድ ደብተራ ስለ ኮከብ ቆጠራ እና ስለጨረቃ አወጣጥ ቀመር አስተምረውኝ ነበር፤ የደብተራ ትምህርት ዳቦ አያበላም ብየ ሳልገፋበት ቀረሁ። የአገራችን ደብተሮች እምቅ እውቀት ቢኖራቸውም እያጣጣልነው ሳንጠቀምበት ቀረን።
ደብተራ ማለት ፊደል የገደለ ከሆነ ታሪኩን ጽፎ ያስቀረ ስንት የእስላም ደብተራስ አለ? በመካከለኛው ክፍለ ዘመን ወደ አማርኛ የተተረጎሙ የሃይማኖት መጽሃፍት በአረብ ደብተራ የተጻፉ ናቸው። ደብተራንስ ማነው አማራ ብቻ ያደረገው? የትግሬ ደብተራም ሞልቷል።
ለታሪካችን የምንሰጠው ዝቅተኛ ቦታ ገና ዋጋ ያስከፍለናል፤ ታሪክ አልባነት የሚፈጥረውን ስሜት ለማወቅ ወደ አንዳንድ የአፍሪካ አገራት ሂዱና እዩት። በ20ኛ ክፍለዘመን መግቢያ ፈረንሳይ ውስጥ እነ ሴዳር ሴንጎር ያቋቋሙት ኔግሪቲውድ የሚባል እንቅስቃሴ ነበር። ኔግሪቲውድ የተመሰረተው ፈረንሳይ ጥቁር አፍሪካውያንን ፓሪዛውያን አደርጋለሁ ብላ ወደ ፈረንሳይ ሰብስባ ካመጣቻቸው በሁዋላ ነው። ጥቁር አፍሪካዊያኑ ፈረንሳይ ከመጡ በሁዋላ ሲያዩት ባዶነት ተሰማቸው፣ የሚወራው ታሪክ ታሪካቸው አልመስል አላቸው፤ ታሪካቸውንና ባህላቸውን ፈልጎ ለማግኘት ተነሳሱ፤ ኔግሪቲውድን ፈጠሩ። ያን ጊዜ የነበሩ ጻሃፎች ሁኔታውን ታቡላ ራሳ (tabular rasa) ብለው ይገልጹት ነበር። በግርድፍ ትርጉሙ፣ ባዶ ሰሌዳ ማለት ነው፤ አዎ የመጡበትን ታሪክ አለማወቅ ጭንቅላትን ጥቁር ሰሌዳ ያደርጋል፤ ጭንቅላትህ ጥቁር ሰሌዳ ከሆነ ደግሞ ነጭ ጠመኔ ( ቾክ) እንደፈለገ ይጽፍብሃል። ያን ጊዜ የምታነበንበው ነጩ ቾክ የጻፈልህን ይሆናል። ራስን ለባርነት አሳልፎ መስጠት ይሉሃል ( ይሉሻል) ይህ ነው።

Thursday, 30 October 2014



ሃብታሙ አያሌው ቶርቸር እየተደረገ ነው !
ክስ ሳይመሰረትበት ለአራት ወራት በማእከላዊ እስር ቤት የሚገኘው የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ወጣት ሃብታሙ አያሌው፣ ከፍተኛ ኢሰብአዊ ግፍ እየተፈጸመበት እንደሆነ ታወቀ። “ወደ ፖለቲካው የማትመለስ ...ከሆነ ትወጣለህ። አለበለዚያ እዚሁ ነው የምትሞተው” በማለት አማራጭ ቢያቀርቡለትም፣ ሃብታሙ መሞትን እመርጣለሁ የሚል መልስ የሰጣቸው ሲሆን፣ እየደረሰበት ባለው ስቃይ በጣም እየታመመ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።
“እስኪ ትግሉን እናስቀጥላለን የሚሉ ሰዎች ያድኑህ ? “ ሲሉ አሳሪዎቹ በስቃዩ የሚደሰቱ ሲሆን፣ ከባለቤቱ በስትቀር ጠበቃዉም ሁሉ ሳይቀር እንዳያየው ተደርጓል። በተመሳሳይ ሁኔታ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ም/ሃላፊ ፣ በታፈነና አየር በማያስወጣ ክፍል ዉስጥ እንዲታሰር በመደረጉ በተደጋጋሚ ለተቅማጥና ተያያዥ በሽታ መጋለጡን፣ እንዲሁም የመተንፈስ ችግር እንዳለበት ለማወቅ ችለናል።
“የፓርቲያችሁ የገንዘብ ምንጭ ምንድን ነው ? አንድነት ዉስጥ ያሉ ጠንካራ አባላት እነማን ናቸው ? “ በሚል ጥያቄ የቀረበለት ዳንኤል ሺበሺ፣ ክብሩን በሚነካ መልኩ እንደሚሰደብም የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ሃብታሙ አያሌው ፣ በእርሱ ላይ እይደረሰ ያለው ግፍ በማንም ዜጋ ላይ መድረስ እንደሌለበት በመግልጽ “የግፈኛው አገዛዝ እንዲያበቃ የኢትዮጵያ ሕዝብ መነሳት አለበት” ሲልም ለህዝቡ የትግል ጥሪ አስተላልፏል
የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ለ 90 ቀናት በተከታታይ በወታደራዊ፣ ፖለቲካዊ እና የመረጃ እና ደህንነት ትምህርቶች ያሰለጠናቸውን ታጋዮች ጥሪ የተደረገላቸው እን...ግዶች እና የተለያዩ የተቃዋሚ ድርጅቶች ተወካዮች በተገኙበት በደመቀ ሁኔታ ባስመረቀበት ወቅት የህዝባዊ ሃይሉ ስልጠና በግንቦት ሰባት ስም ከሚደረጉት ስልጠናዎች የመጨረሻው መሆኑ ተመልክቷል።
ህዝባዊ ሃይሉ ለኢሳት በላከው መግለጫ የህዝባዊ ሃይሉ ዋና አዛዥ ኮማንደር አሰፋ ማሩ ‘’ህዝባዊ ሃይላችን በኢትዮጵያ ውስጥ የተንሰራፋውን ዘረኛና አፋኝ የወያኔ ስርዓት ከህዝብ እና ከሃገራችን ጫንቃ ላይ አስወግዶ በምትኩ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለመገንባት ከተመሰረተ ጀምሮ ባለፉት ጊዚያት በርካታ ስራዎችን በመስራት አስተማማኝ ድርጅታዊ አቋም ላይ ይገኛል’’ ማለታቸውን ጠቅሷል።
የኢትዮጲያ ህዝብ አርበኞች ግንባር፣ የአማራ ዴሞክራሲያዊ ሃይል ንቅናቄ እና የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ተዋህደው ባንድ ድርጅት ጥላ ስር ትግላቸውን አስተባብረው ለመታገል የሚያደርጉትን የውህደት ሂደት የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ ባደረሱበት ወቅት ላይ መርቃቱ መደረጉን ያወደሱት ኮማንደሩ፣ የህዝባዊ ሃይሉ ስልጠና በግንቦት ሰባት ስም ከሚደረጉት ስልጠናዎች የመጨረሻው እንደሚሆንም ተናግረዋል።
ኮማንደሩ ‘’ስልጠና ለአንድ ታጋይ የትግሉ የመጀመሪያ ምዕራፍ ሲሆን በስልጠና ላይ ያገኛችሁትን ትምህርት በተግባር ለቆምንለት ዓላማ እና ተልዕኮ በቁርጠኝነት እንደምታውሉት ሙሉ እምነቴን እገልጻለሁ‘’ በማለት ለስልጠናው መሳካት የተለያዩ ድጋፎችን ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
የግንቦት7 ህዝባዊ ሃይል ከዚህ ቀደም 4 ተከታታይ ምርቃቶችን ማካሄዱ ይታወሳል።

Monday, 27 October 2014


ዓረና በዓዲግራት....!
===========
ከአንዶም ገብረስላሴ
...
ዓረና ትግራይ ባለፈው ዓመት በዓዲግራት ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ ጠርቶ እንደነበርና የህወሓት ፋሺሽታዊ ተግባር በጠራራ ፀሃይ የተጋለጠበት ኣጋጣሚ መፍጠሩ ያሚታወስ ነው።
በህዝባዊ ስብሰባው እኔ ‪#‎Amdom‬,‪#‎abraha‬ ፣ato asgede ና ሌሎች ኣባሎቻችን በፖሊሶች ፊት ተደብድበን ህዝቡ በህወሓት መሪዎች የነበረችው ትንሽ ተስፋ ጨርሶ ያጣበት ኣጋጣሚ ነበር።
ዓረና ከዛ ፋሽሽታዊ የህወሓት ተግባር በሗላ በዓዲግራት ከተማ ትልቅ የሚባል ህዝባዊ ማነሳሳት ኣላካሄደም ነበር።
ዛሬ ሰኞ 17 / 02 / 2007 ዓ/ ም የዓረና ኣባላት የፓርቲው ኣማራጭ ፖሊሲዎችና የመፍትሄ ሃሳቦች የያዘ በራሪ ፅሁፍ ሲያድል ወለዋል።
በዛሬው ቀን የዓጋመና የዓዲግራት ህዝብ በከተማው የተፈፀመው የህወሓት ፋሽሽታዊ ተግባር ክፉኛ እንዳሳፈረውና እንዳናደደው በራሪው ፅሁፍ ስንሰጠው ይሰጠን የነበረ ኣስተያየት ኣመላካች ነበር።
ኣንድ ምሳሌ ልጥቀስላቹ ኣቶ ፀሃዬ የተባለ የድሮ ታጋይና የሰለሞን ሆቴል ባለበት የዓረና ኣባላት በሆቴሉ ኣልጋ ይዘው ኣደሩ።
ጥዋት በራሪ ፅሁፋችን ለማደል ኣዲሱ የዓረና ብርቱኳናማ ቲሸርት ለብሰን ስንንቀሳቀስ ዝምብሎ ያየን ነበር። ትንሽ ረፈድ ሲል ከህወሓት ካድሬዎች ስልክ ተደዉሎ የተለያዩ ዛቻዎች ወረዱበት።
በካድሬዎቹ ዛቻ ክፉኛ የደነገጠው ፀሃየ በሆቴሉ ሻይ ኣዝዞ ለነበረው የዓረና ኣባል በማዋከብና የስድብ ውርድብኝ በማዝነብ ከሆቴሉ ኣስወጣው። ከዚህ ኣልፎም "..ንዓረና ቦታ ኣይንህቦን(ለዓረና ቦታ ኣንሰጠውም)፣ ቃልስና ነዊሕን መሪርን እዩ ዓወትና ናይ ግድን እዩ ( ትግላችን ረዥምና መራራ ነው፣ ድላችን የግድ ነው።.." የሚል በሆቴሉ ደጃፍ ለጠፈ።
ይህ ሁሉ ይከታተሉ የነበሩ ወጣቶች ፀሃየን ክፉኛ በመውቀስ "...እኛ ኣማራጭ እንፈልጋለን፣ እነዚህ ሰዎች የራሳችን ወገኖች ናቸው፣ ከየትም ኣልመጡም የት እንዲሄዱ ነው የምትፈልገው? ባለፈው ዓመት የሰራቹት ኣፀያፊ ተግባር ኣሁንም ለመድገም መሞከራቹ ነው?.." ወዘተ የሚሉ ምክሮች በመለገስና ኣቋሙ እንዲያስተካክል ጥረት ኣድርገዋል።
የህዝቡ ጥያቄ "...ዓረና በዓዲግራት ህዝባዊ ስብሰባ እንዲያካሂድ..." የሚል ነበር። ዓረናም ኣማራጭ ሃሳቡ ለዓጋመና ዓዲግራት ህዝብ በማቅረብ ጠቃሚ የውይይት መድረክ እንደሚያዘጋጅ ቃል ገብተንላቸው ተመልሰናል።
በዓዲግራት ከተማ በራሪው ፅሁፍ እያደሉ ከነበሩ 3 ቡድኖች የኣንዱ ክንፍ በምስሉ የሚታዩት ናቸው።
በዓዲሱ ዓመት የዓረና በራሪ ፅሁፍ በኣላማጣና ሌሎች 4 የራያ ዓዘቦ ቀበሌዎች፣ ውቕሮ፣ ዓብይ ዓዲ፣ መቐለ፣ ኲሓ፣ ኣይናለም ዛሬም በዓዲግራት ከተሞች ለህዝቡ ኣዳርሷል።
ነፃነታችን በእጃችን ነው...!
IT IS SO...!

የአብርሃ ደስታ ሁኔታ አሳሳቢ ነው
====================
አብርሃ ደስታ ጥላቻን በፍቅር የሚታገል፤ ከስሜት ይልቅ ምክንያት የሚያስቀድም፤ ከብሄርተኝነት ይልቅ ለሰው እና ለሰብአዊነት ልዩ ክብር ያለው፤ የብሄር አጥር በጣጥሶ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለሁ...ለንተናዊ ለውጥ በጋራ እንዲሰለፍ ብዙ መስዋእት የከፈለ የዘመኑ ዘመናዊ ማንዴላ ነው፡፡
የኔ ትውልድ ካፈራቸው ምርጥና ምጡቅ ፖለቲኮኞ አንዱና ምናልባትም ግምባር ቀደሙ አብርሃ ደስታ ነው፡፡ አብርሽ ኢሰብኣዊነትን በእውቀቱና በብእሩ በሰላማዊ መንገድ ብቻ የሚታገል ምርጥ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ ልክ የ60ዎቹ ትውልድ ተብለው የሚጠሩት እነ ሀይለ ፊዳ፣ ብርሃነ መስቀል ረዳ ፣ ጌታቸው ማሩ ፣ ጥላሁን ግዛው….ምርጥ ወጣቶች ተብለው እንደሚጠሩ ሁሉ አብርሃ ደስታ፣በቀለ ገርባ፣ ሃብታሙ አያለው፣ ….የአሁኑ ትውልድ ምርጥ ወጣቶችና የትውልዱ ውጤቶች ናቸው፡፡ እነዚህ ጀግኖች ሰው አይደለም አይጥም ሳይገድሉ ነው ወደ ወሀኒ የተወረዎሩት፡፡ አንዳች ንብረትም አላወደሙም፡፡ ሀጥያታቸው ፍቅርን መስበካቸውና አምባገነንነትን በማርያም መንገድ መታገላቸው ብቻ ነው፡፡
የስርዓቱ ሰላማዊ ተቀናቃኝ ፖለቲከኞች ለማጥመድ ሆንተብሎ የፀደቀው የፀረሽበር ህግ አብርሃ ደስታ ያለ አንዳች መረጃ አጥምዷል፡፡ ፖሊስ እስከ አሁን ያቀረበው ጠብ የሚል መረጃ የለም፡፡ ሁሌ ተጨማሪ ጊዜ ይሰጠኝ እያለ ሰውን እያሸ ነው፡፡ ወጣቱ ፖለቲከኛ በሃሰት ለማስወንጀል በመቀሌ የተደረጉ አሳፋሪ ደራማዎችም አይተናል፡፡ ዓረና ትግራይ ህወሓት ያደረጋቸው እያንዳንዷ እርምጃ እግር በግር እየተከታተለ ነው፡፡ ጊዜው ሲደርስ ከነጭብጦቹ ይፋ ይደረጋል የሚል ግምት አለኝ፡፡
ከወደ ሰሞኑን ደግሞ ለአበርሀ ምግብ እያመላለሰች ስትጠይቀውና ስትከታተለው የነበረች የአክስቱ ልጅ እንዳትጠይቀው ተከልክላለች፡፡ እቺ እህታችን ከዚህ በፊት በሳምንት አንድ ጊዜ እንድታገኘው ተፈቅዶላት ትጠይቀው ነበር፤ አሁን ግን ከእናቱ፣አባቱ፣ወንድሙ፣እህቱ ውጪ ሌላ ማንም ሊጠይቀው አይችልም አንቺም አትችይም ተብላለች፡፡ የአብርሀ ቤተሰቦች ደግሞ ውክልና ለሷ ነው የሰጧት፡፡ ቤተሰቦቹ በሀውዜን ስለሚኖሩ ሊከታተሉትም ሊጠይቁትም አይችሉም፡፡ ልትጠይቀውም ልትከታተለውም የምትችለው በአደስ አበባ የምትኖረው የአክስቱ ልጅ ብቻ ናት፡፡ ከዚህ የተነሳ መላ ቤተሰቡ ተጨንቀዋል፡፡ ይህ ወጣት ፖለቲከኛ ከሌሎች የህሊና እስረኛች በተለየ መልኩ ጫና እየተደረገበት ነው፡፡ ሌሎች በየ ቀኑ እንዲጠየቁ ተፈቅዶላቸው አብርሃ ግን ያቺ በሳምንት አንዴም ተከልክሏል፡፡ እናም ወንድማችን እኛም ቤተሰቦቹም በምን ሁኔታ እንዳለ ማወቅ አልቻልንም፡፡ ብርታቱ እና ፅናቱ ይስጠው፡፡
እስራት የጀግኖቻችን ማጎሪያ በሆነበት ስርዓት እንደ ተሜ አይነት ሀገር ወዳድ የሆኑ ቆራጦች በይስሙላ የፍትሕ ስርዓት በግፍ ወደ ማጎሪያ ማዕከል መግባታቸዉ የስርዓቱን አይን ያወጣ አምባገነንነትና ሗላ ቀርነት ፍንተዉ አድርጎ የሚያሳይ ነዉ።ታድያ ሁሉም ኢትዮዽያዊ በታሰረበት አገር ነጻዉ ማን ነዉ???በኔ ምልከታ ያልታሰረዉ የህብረተሰብ ክፍል ስለ ሀገሩና ህዝቡ ግድ የሌለዉ ብቻ ነዉ።ልብ ይበሉ! ተመስገን የታሰረዉ የመናገር፤የመጻፍ፤ሀሳብን የመግለጽ ዼምክራሲያዊናህገ መንግስታዊ መብት የሚለዉን እንተወዉና ተፈጥሯዊ ወይም ሰብ አዊ መብቱን ተገፎ ነዉ።ሞት ላሳዳጁና ለግፈኛዉ የወያኔ ስርዓት ነጻነት ሳይተነፍስ በቁሙ ለሞተዉ ሰፊዉ ህዝብ

Sunday, 26 October 2014

የኢትዮጵያን የአየር ክልል ያለፈቃድ ጥሰው የገቡ አምስት የሱዳን ሔሊኮፕተሮችና 26 አብራሪዎቻቸው ታስረው መለቀቃቸውን የታጋይ አማረ አረጋዊ ንብረት የሆነው ሪፖርተር ጋዜጣ ዘገበ
ሩሲያ ሠራሽ የሆኑት አምስት የትራንስፖርት ሔሊኮፕተሮች ንብረትነታቸው ተቀማጭነቱ ሱዳን ካርቱም የሆነ ሔሊኮፕተር አከራይ ኩባንያ ነው፡፡ ኩባንያው በሱዳን ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን የተመዘገበ ሆኖ፣ በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች የበረራ አገልግሎት ይሰጣል፡፡ አብራሪዎቹ ግን ምሥራቅ አውሮፓውያን ናቸው ተብሏል፡፡
ምንጮች ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ከሦስት ሳምንት በፊት አምስቱ ሔሊኮፕተሮች የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣንን ሳያስፈቅዱ ከካርቱም ወደ ባህር ዳር ጉዞ ይጀምራሉ፡፡ ሔሊኮፕተሮቹን የተከራየው የታንዛኒያ መንግሥት ሲሆን፣ አብራሪዎቹ ዓላማቸው ከካርቱም በኢትዮጵያን አ...ድርገው፣ ኬንያ በመቀጠል ወደ ታንዛኒያ ማቅናት ነበር፡፡ ባህር ዳር አርፈው ነዳጅ ቀድተው ጉዟቸውን ለመቀጠል አቅደውም ነበር፡፡
ይህን ሁሉ ሲያቅዱ ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከተው የበረራ ፈቃድ (የኢትዮጵያን የአየር ክልል ለማቋረጥ ወይም ኢትዮጵያ ውስጥ ለማረፍ) የሚሰጠውን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽንን አላነጋገሩም፡፡ ጉዳያችሁን አስጨርሳለሁ ያላቸውን አንድ የባህር ዳር ነዋሪ በሰጣቸው የመተማመኛ ቃል ብቻ ይዘው፣ የኢትዮጵያን የአየር ክልል በአማራ ክልል በኩል ጥሰው ገብተዋል፡፡
ጉዳዩን በከፍተኛ ንቃት ሲከታተል የነበረው የኢትዮጵያ አየር ኃይል የሰሜን ዕዝ የአየር መቃወሚያ ክፍል፣ ሔሊኮፕተሮቹን ዒላማ ውስጥ አስገብቶ ሲቃኛቸው እንደነበር ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን የአየር ትራፊክ መቆጣጠሪያ ባለሙያዎችም በአገር አቀፍ ራዳር ሲከታተሏቸው እንደነበር ታውቋል፡፡
አምስቱም ሔሊኮፕተሮች በተሰጣቸው ትዕዛዝ መሠረት ባህር ዳር ግንቦት 20 ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ በሰላም አርፈዋል፡፡ ‹‹ሔሊኮፕተሮቹ የሲቪል እንደሆኑ በመታወቁ በተዋጊ ጄቶች ማጀብ አላስፈለገም፤›› ብለዋል ምንጮች፡፡
ባህር ዳር እንዳረፉ ከሔሊኮፕተሮቻቸው በቀጥታ ወደ መኪና ገብተው በኢትዮጵያ ፀጥታ ኃይሎች ታጅበው ወደ ማረፊያ ቤት መወሰዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ባለሙያዎች በአብራሪዎቹ ላይ ምርመራ ማካሄዳቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ አብራሪዎቹ ያለፈቃድ የአንድ ሉዓላዊ አገር የአየር ክልል አልፈው በመግባታቸው የአማራ ክልል ዋና ከተማ ባህር ዳር በሚገኘው የክልሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
በተካሄደው ምርመራ አብራሪዎቹ ሌላ ተልዕኮ ኖሯቸው ሳይሆን በተሳሳተ አካሄድ ባህር ዳር አርፈው ነዳጅ ሞልተው ጉዟቸውን ወደ ታንዛኒያ ለመቀጠል በማቀድ ነው የሚል መተማመኛ ላይ በመደረሱ፣ ባለፈው ሳምንት አምስቱ ሔሊኮፕተሮችና 26 አብራሪዎች ተለቀው ከአገር መውጣታቸውን ምንጮች አረጋግጠዋል፡፡
አብራሪዎቹ የተለቀቁት በዋስትና ሲሆን በቀጠሮአቸው ቀን ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ አዲስ አበባ የሚገኙ የሱዳን ዲፕሎማቶች አብራሪዎቹን ለማስለቀቅ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ ጉዳዩ በፍርድ ቤት የተያዘ ቢሆንም፣ በዲፕሎማሲያዊ ውይይት መፍትሔ ሊያገኝ እንደሚችል ምንጮች ያላቸውን ግምት ገልጸዋል፡፡
ባህር ዳር አርፋችሁ ነዳጅ እንድትቀዱ ተፈቅዶላችኋል ብሎ ያሳሳታቸው ግለሰብ በቁጥጥር ሥር እንደሚገኝም ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሔሊኮፕተሮች ነዳጅ የመያዝ አቅማቸው ውስን በመሆኑ ረዥም በረራ በሚያደርጉበት ወቅት በየቦታው በማረፍ ነዳጅ ይቀዳሉ፡፡ አንድ ሔሊኮፕተር በአማካይ በሰዓት 800 ሊትር ነዳጅ እንደሚጠቀም ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ኃላፊዎች ስለጉዳዩ የምናውቀው ነገር የለም ብለዋል፡፡ የሱዳን ኤምባሲን በስልክ ለማነጋገር የተደረገው ሙከራ አልተሳካም፡፡
በ1992 ዓ.ም. ያለፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ የአየር ክልል የገባ ዕቃ ጫኝ አውሮፕላን በኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አየር መከላከያ ምድብ በተተኮሰ ቮልጋ ሚሳይል ተመትቶ መጋየቱን ያስታወሱት ምንጮች፤ ‹‹የኢትዮጵያ አየር ክልል እንዲያው ዝም ብሎ ዘው ተብሎ የሚገባበት አይደለም፤›› ብለዋል፡፡
በዚያን ወቅት አውሮፕላኑን ያበሩ የነበሩ ሁለት የስዊድን ዜግነት ያላቸው ፓይለቶች ሕይወታቸው አልፏል፡፡ አውሮፕላኑ ከአሜሪካ በኪራይ የመጣ ሲሆን ወደ ሞዛምቢክ እየተጓዘ ነበር፡፡ ወደ ኢትዮጵያ ከማቅናቱ በፊት አስመራ አርፎ ነዳጅ ቀድቶ ነበር፡፡
ታላቁ የሀገራችን ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም Democracy for Ethiopia sport Group’ የተሰኘው መቀመጫውን በአወስትራሊያ ያደረገው ቡድን ያዘጋጀውን የእድሜ ዘመን ስኬት ሽልማት ለመቀበል ሰሞኑን ወደ አውስትራሊያ መሄዳቸው የሚታወቅ ሲሆን ይህንም ተከትሎ በሚልቦርን፣ በሲድኒ፣ በብሪስባኔና በሌሎች የአውስትራሊያ ከተሞች ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጋር በአገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት እያደረጉ እንደሚገኙ ከስፍራው የደረሠኝ መረጃ ያስረዳል፡፡
ፕሮፌሠር ለዚህ ሽልማት ያበቃቸው በሁለቱ አምባገነን መሪዎች ማለትም በመንግስቱ ሐ/ማርያም እና በመለስ ዜናዊ የስልጣን ዘመኖች ከህዝብ ወገን ቆመው ህዝባዊ ወገንተኝነት በማሳየታቸው እንዲሁም ባለፉት 50 አመታት ሐገራችን እየተጓዘችበት ያለውን የኋሊዮሽ ጉዞ ለማስቆም ባደረጉት ጥረት ነው፡፡
ፕሮፌሠር መስፍን የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች እና የጂኦግራፊ ምሁር ሲሆኑ በርካታ ሐገራዊ መፅሐፍትን የፃፉ በሠላ ብዕራቸው ገዢው ፓርቲ ይስተካከል ዘንድ ሐሳቦችን የሚያቀርቡ ለወጣቶች አርአያ የሚሆኑ ታላቅ የሐገራችን ምሁር ናቸው
ክብር ለፕ/ር መስፍን  ወልደማርያም እና ስለሐገራቸው ስለኖሩ ምሁራኖቻችን

Tuesday, 14 October 2014

ስለ ተመስገን ደሳለኝ
ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ
(ቀደም ብዬ መፃፍ የነበረብኝ ሀሳብ)...
ዛሬ ከደቂቃዎች በፊት የተመስገንን መታሰር ስሰማ አዘንኩ ። "በምንና እንዴት ታሰረ? መታሰሩ አግባብ ነው? " የሚለውን አላነሳም ። ምክንያቱም ከግምት የተሻለ እውቀት የለኝም ። አሁንም በቀጠሮው ቀን ምን እንደሚል አላውቅም ። ይህ ሀሳቤም አሁን ተመስገን ካለበት ሁኔታ ጋር አይገናኝም ። ይሁንና ቀደም ሲል መፃፍ የነበረብኝን ሀሳብ ላንሳ ።
ተመስገን ፋክት መጽሔት ላይ እንድጽፍ ሲያነጋግረኝና ከዚያ በፊት ለእሱ የነበረኝ ግምት የተለያየ ነው ። አራት ኪሎ አግኝቼ ያናገርኩትና ፋክት እስክትቆም ያየሁት ተመስገን ለእኔ እንዲህ ነው ።
የሚጮህ ጽሁፍ የሚጽፈው ተመስገን በጣም ጸጥተኛ ነው ። ደፋሩን ጸሀፊ የትህትና ፍርሀት ያለበት ሆኖ ነው ያገኘሁት ። ለስላሳነቱ የውስጥ ባህሪው ነው ። ከሁሉም በላይ በግል እንደራሴም ይሁን እንደ ሙያውን ወዳድ ጋዜጠኛ ፍጹም ነጻነት የሰጠኝ ከሁሉም በላይ ተመስገን ደሳለኝ ነው ። አብረን ለመስራት ተስማምተን ስለጽሁፍ ይዘት ስናወራ "ምን አይነት ይዘት ያለው ጽሁፍ እንድጽፍ ነው የምትፈልገው?" ስለው የሰጠኝ መልስ መቼም የማልረሳውና በአንዱ የመጽሔቱ እትም ላይ የጻፍኩት ነው ። " እንዲህ ጻፍ አልልህም ። የፈለከውን ጻፍ ። ኢህአዴግ በአለም ላይ ታይቶ የማይታው ዲሞክራሲ አምጥቷል ብለህ ካመንክ የመጻፍ መብት አለህ ። አንተ ስም ስላለህ ድጋፉንም ተቃውሞውንም የምትቀበለው ራስህ ነህ " አለኝ ። ይህ ለአንድ ጋዜጠኛ ፍፁማዊ ነጻነት ነው ። ተመስገን ደሳለኝ ከጥሩ የብር ክፍያው ጎን ይህን ከፍሎኛል ። የትም ብሄድ ይህን ነጻነት አላገኘውም ። በፋክት መጽሔት ቆይታዬም ከቃለመጠይቅ ጀምሮ እስከ መጣጥፎች በዚህ ነጻነት ነው የሰራሁት ። አንድም ቀን በዚህ ርዕስ ላይ ብትፅፍ ያላለኝና በሀሳቤ ጣልቃ ያልገባ ሰው ይህ ሰው ነው ። መጻፍ ሲገባኝ ያልጻፍኩት ወይም ያልተገባ ሀሳብ ጽፌ ከተገኘሁ በራሴ ግፊትና ሀሳብ ነው ። ለጻፍኩት ሁሉ ሀላፊነቱን የምወስደው እኔ ብቻ ነኝ ። ማንም ሌላ የለም ። ይህን የጋዜጠኛ ነጻነት ሌላ ቦታ አገኘዋለሁ ብዬ አላምንም ። በዚህ ተመስገንን ሁሌም አከብረዋለሁ ። እውነት ለመናገር መቼም ወደ ፕሬስ ስራ ቢመለስ አብሬው ለመስራት የማላመነታው አንድ ሰው ይህ ዛሬ ታሰረ የተባለው ተመስገን ደሳለኝ ነው ። ለእኔ ለጋዜጠኛው ከመጽሔቱ ሰውየው ተመስገን ይበልጥብኛል ። እጄን ይዞ ሊያጽፈኝ የማይሞክር የነጻነት አለቃዬ ነው ። አክባሪዬም ነው ተመስገን ። ለእኔ ግን ከማክበሩም በላይ ነጻነቱ ይበልጥብኛል ። አሁንም ልድገመውና ተመስገን ነፃ ወጥቶ ወደ ፕሬስ ስራ ቢመለስ እስከ ነጻ ባለ ክፍያ አብሬው ለመስራት የምፈልገው ሰው ነው ። ነጻነት በራሱ ክፍያ ነው ። ተመስገን ደግሞ ይህን እንደሚከፍለኝ አምናለሁ ።
አምላክ በድጋሚ በስራ እንደሚያገናኘን ፀሎቴ ነው ።


የመጀመሪያው ፎቶ፡ በአዲስ አበባ የሳውዲ አረቢያ ኢንባሲ ባሳለፍነው አመት ወገኖቻችንን በሳውዲ አረቢያ መገደላቸውን፤ መታሰራቸውንና ሴት እህቶቻችን መደፈራቸውን በመቃወም የአዲስ አበባ ህዝብ ለተቃውሞ ሲወጣ በወያኔ ፖሊሶች እያሯሯጡ ሲደበድቡዋቸውና ሲበታትኗቸው ያሳያል

ሁለተኛው ፎቶ፡ በቅርቡ በአሜሪካ ዋሽንግተን ዲስ የወያኔን ኢንባሲ ኢትዮጵያውያን መቆጣጠራቸውንና የተሰቀለውን የወያኔ ሰንደቅ አላማ በማውረድ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ባንዲራ መስቀላቸውን በመቃወም በኢትዮጵያ አሜሪካ ኢንባሲ ፊት ለፊት ለተቃውሞ የወጡ (የወያኔ ደጋፊዎችን!?!) ያሳያል

እርስዎስ እስኪ ፎቶዎች በመመልከት የተሰማዎትን ስሜት ወይም ፍርድ ይስጡ!

Saturday, 11 October 2014

የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ በደህንነት ሰዎች ተደበደቡ
***********************************
የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የሰሜን ቀጠና ኃላፊ የሆኑት አቶ አዕምሮ አወቀ ሐሙስ ዕለት ከሥራ ወደ ቤታቸው ሲጓዙ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ለፍኖተ ነፃነት ገለጹ፡፡ እንደ አቶ አዕምሮ ገለፃ ይህ ድርጊት በየጊዜው እንደሚከሰትና በሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት እንቅስቃሴ በደሴ ከተማ በመኪና ለማፈን በተደረገው ግብግብ መኪና ውስጥ አስገብተው እንደተደበደቡ ራሳቸውን ለመከላከል በሚታገሉበት ወቅትም ጋቢና የተቀመጠውን ሹፌር መኪናውን ለማስነሳት ቁልፍ እንደያዘ እጁን ሲረግጡት በመጎዳቱ፣ ሁለቱ ከኋላ የያዟቸውን ደህንነቶች ለመከላከል ባደረጉት ግብ ግብ ስላየሉባቸው ገፍትረው ከመኪናው እንደጣሉዋቸውና ወደ አዲስ አበባ ከመጡም... በኋላ ወንድማችንን ደብድበሃል የትም አታመልጥም በሚል ለገሃር አካባቢ በቡድን ድብደባ እንደፈጸሙባቸው ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ከሰሜን የሚመጡ የፓርቲው አባሎችን ለመቀበል ዝግጅት በሚያደርጉበት ታህሳስ 17/2006 ዓ.ም ቤታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተሰብሮ ንብረቱ በሙሉ ከቤት ተጭኖ ተወስዷል፡፡ ሐሙስ ዕለትም ከሥራ ወጥተው በትራንስፖርት ወደ ቤታቸው በሚሄዱበት ወቅት አየር ጤና አካባቢ ከአውቶቡስ ሲወርዱ ሁለት ደህንነቶች ግራና ቀኝ እጃቸውን በመያዝ እንዳይንቀሳቀሱ ካደረጉዋቸው በኋላ ሦስተኛው ደህንነት በድንጋይ ከጉልበታቸው በታች ደጋግሞ በመምታት ቀኝ እግራቸው ላይ ጉዳት አድርሰው ሦስቱም ከአካባቢው እንደተሰወሩ ገልጸዋል፡፡ ይህ ህገ ወጥ ድርጊት በሰላማዊ መንገድ ለውጥ እንዲመጣ መታገሌን እንዳቆም እንደማያደርገኝ ሊያውቁት ይገባል በማለት ለፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል ገልጸዋል፡፡

የኢህአዴግ ባለስልጣናት ስጋት ጨምሯል። ስብሰባ ማብዛት መፍትሄ አልሆነም።

☞ «ተቃዋሚዎች ተንሰራርተዋል… ሕዝቡ እንዳይውጠን መጠንቀቅ አለብን»
☞ የተጀመረው ትግል ፍሬያማነቱ እየታየ ስለሆነ ተቃዋሚዎች እና ሕዝቡ በንቃት በጋራ መሳተፍ አለባቸው።
☞ የባለስልጣናቱ ተስፋ እየተመናመነ ስለሆነ ሕዝቡ ትግሉን ማጠናከር ይጠበቅበታል።
የወያኔ ባለስልጣናት በስልጣን የመቆየት ፍላጎታቸው ላይ የተደነቀረው የህዝብ አቤቱታ እና የተቃዋሚዎች መንሰራራት ስጋት እንደሆነባቸው ታውቋል። ህዝቡ በጎሪጥ እያየን ያለበት ሁኔታ ተቃዋሚዎች አንድ እርከን አንሰራርተው መታየታቸው እንዲሁም ዲያስፖራው ጥርሱን ነቅሶ በነቂስ እየተቃወማቸው እንደሆነ ከዚህም በተጨማሪ ስልጠና ብለው በጠሩበት ቦታ ላይ ሁሉ የደረሰባቸው ተቃውሞ ሕዝባዊ ጥያቄ እና አስተያየት እጅግ አሳሳቢ እንደሆነ ተወያይተዋል።
እንደ አዲሱ ለገሰ እምነት የተቃዋሚዎች መንሰራራት እና የህዝቡ ጥያቄ መፍትሄ ካልተፈለገለት በስተቀር እንደበሰበስን ማወቅ አለብን። በአሁን ወቅት እያየነው ያለነው ነገር ሕዝቡ ምን ያህል እንደተንገሸገሸ እና በጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደከተተን ከስልጠናዎች የሚመጡ ሪፖርቶች ብቻ በቂ ናቸው። ከየቦታው በየጊዜው የሚሰበሰበው ሪፖርት ከታየ ከዚህ በበለጠ ምን ያህል በስብሰን ልንወድቅ እንደቀረብን ያሳያል። ብለዋል የኢህአዴግ የጀርባ አጥንቶች የሚባሉ አንጋፋ እና ታማኝ የሚባሉ ታጋዮች በተሰባሰቡበት ስብሰባ ውይይት ላይ። ህዝቡ ሊውጠን ይችላል ስልጠናዎች ላይ የታዩ ሂድቶች ይህንን አመላካች ናቸው። ብለዋል።
በተቃዋሚ ሃይሎች ውስጥ የመደብናቸው ሰዎቻችን ስጋት ላይ ናቸው። ምንም አይነት መረጃዎችን ይዘው አይመጡም ፍሬ ከርስኪ ወሬ ነው የሚያወሩት የሕወሓት ሰዎችን እንዳንመድብ ሕዝቡ በትግሬዎች ላይ ያለው ጥርጣሬ በፍጹም እንዳይተነፍስ ሆኗል። የምንከፍላቸው የተቃዋሚ አመራሮችን ከሃገር የሚወጡበት መንገድ ከማመቻቸት ውጪ ምንም ሲፈይዱ አላየንም። ከወጡ በኋላ የተለያዩ መረጃዎች እያፈተለኩ ያሉበት ሁኔት እየታየ ነው። የገዛናቸው ተቃዋሚዎች ሳይቀሩ በዘረፋ ተክነው ከሃገር ውጪ እየሸሹ ስለሆነ ሕዝቡ እንዳያበላሸን መጠንቀቅ አለብን ሲሉ የጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪ ጸጋዬ በርሄ ተናግረዋል።
ወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣናቱ በውጥረት እና በስጋት ላይ መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮች ስርአቱ እንደበሰበሰ እና በጉልበት እንዲሁም በምእራባውያን ሃይል እየኖረ እንዳለ ተነጋግረውበታል። የምእራባውያን ድጋፍ ጥሩ ያለ ቢሆንም እያበሰበሰን እና እየገደለን ነው ያሉት ባለስልጣናት በፖለቲካ ድርጅቶች ላይ ከፊል ገደብ እንዲጣል ተስማምተዋል። ከመጀመሪያው የትኛውን መብት ለፖለቲካ ድርጅቶች እንደሰጡ እንኳን ያልተረዱት ባለስልጣናት ፓርቲዎቹ እንዳይንቀሳቀሱ አድርገው ሳለ ከፊል ገደብ እንጥላለን ማለታቸው ባዶነታቸውን በገሃድ ያመላክታል ሲሉ ምንጮቹ ገልጸዋል።
ኢሕአዴግ እንደበሰበሰ በይፋ ያመኑት አቶ አዲሱ ለገሰ እና አቶ ጸጋዬ በርሄ በንግግራቸው ውስጥ ስለመጭው ጊዜ ከባድ ፍርሃት ይነበብባቸው ነበር ሲሉ የገለጹት ምንጮች ተቃዋሚ ፓርቲዎች የጀመሩትን ትግል አጠናክረው ከቀጠሉ ኢሕአዴግ ምንም አይነት ተስፋ እንደሌለው እና ምእራባውያንም ቢሆን የተቃዋሚዎችን ጥንካሬ እና በትግሉ መግፋት ካዩ ወደ ተቃዋሚው ጎራ የማይገለበጡበት አንዳችም ምክንያት የለም ሲሉ ምንጮቹ ኢህአዴግም ቢሆን ይህንን ጠንቅቆ ያውቀዋል ሲሉ አስረግጠው ተናግረዋል።
ዋ/ሥራ አስኪያጅ አቡነ ማቴዎስ: ፓትርያርኩ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ከቅ/ሲኖዶሱ ያጡትን ይኹንታ በአቋራጭ ለማግኘት ‘በመልካም አስተዳደር’ ስም የጠሩትን ስብሰባ ተቃወሙ!
ስብሰባው ፓትርያርኩ ‹‹አጥፍቸው እጠፋለኹ›› ባሉት ማኅበረ ቅዱሳን ላይ ቅስቀሳ በማካሔድ በቅዱስ ሲኖዶሱ ላይ ጫና ለማሳደርና ለኃይል ርምጃ ምቹ ኹኔታ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡
* * *
- ‹‹ባላወጣነውና ባላጸደቅነው ሕግ ማኅበራትን መፈረጅና ሕገ ወጥ ማለት አንችልም፡፡››
- ‹‹አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎች ክፋት ዕድሜያቸውን አሳጥረዋል፤ ቅዱስነትዎም ያስቡበት፡፡››
= ‹‹ከአለቆችና ጸሐፊዎች ጋራ የተደረገው ውይይት አባቶች የተዘለፉበትና ያዘኑበት ነው፡፡››
= ‹‹ለእገሌ ሚኒስትር እናገራለኹ፤ ለእገሌ ደኅንነት እደውላለኹ እያሉ አያስፈራሩን!!››
/ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ/
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤ በፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ተጠርቶ መስከረም ፳፯ እና ፳፱ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. የተካሔደው ስብሰባ የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ወቅታዊ ኹኔታ የማይገልጽ፣ መዋቅሩን ያልጠበቀ እና ጽ/ቤታቸው የማያውቀው መኾኑን በመግለጽ ተቃወሙ፡፡
‹‹የቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊ አስተሳሰብ ማበልጸግ›› በሚል ርእስ ከትላንት በስቲያ በመንበረ ፓትርያርኩ አዳራሽ የግማሽ ቀን ስብሰባ በተደረገበት ወቅት፣ የፓትርያርክ አቡነ ማትያስን የመግቢያ ንግግር ተከትለው ቅድሚያውን በመውሰድ የተናገሩት ዋና ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ÷ ‹‹አኹን ወደ ስብሰባው ስገባ ነው መልእክቱን የሰማኹት፤ አጀንዳውም ከመቅረቡ በፊት ከቋሚ ሲኖዶሱ ወይም ከእኔ ጋራ ምክክር አልተደረገበትም፤›› በማለት ስብሰባው መዋቅሩን ሳይጠብቅና ከዕውቅናቸው ውጭ የተጠራ እንደኾነ ተናግረዋል፡፡
የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት አስተላልፎታል በተባለው የቃል ትእዛዝ መጠራቱ በተገለጸው በዚኹ ስብሰባ÷ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የመምሪያዎች ዋናና ምክትል ሓላፊዎች፣ የየመምሪያው ዋና ክፍሎች ሓላፊዎች፣ የድርጅቶች ዋናና ምክትል ሥራ አስኪያጆች፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ሓላፊዎች፣ የዋና ክፍሎችና የክፍሎች ሓላፊዎች፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤቶች ዋናና ምክትል ሥራ አስኪያጆች መሳተፋቸው ተገልጧል፡፡
በ፳፻፩ ዓ.ም. በቅ/ሲኖዶስ ውሳኔ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የመልካም አስተዳደር እንቅስቃሴ መቀጣጠሉን ተከትሎ የቀድሞው ፓትርያርክ መዋቅሩን ሳይከተሉና ከቅ/ሲኖዶሱ ጋራ ሳይመክሩ ወስደዋቸው ነበር ያሏቸውን ርምጃዎች በመቃወም በወቅቱ የኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ የነበሩት የአኹኑ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የሰጡት ቃለ ምልልስ በማስረጃነት ተይዞ እንደሚገኝ ያስታወሱት ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ‹‹ቅዱስነትዎ በምትካቸው ሲቀመጡ መዋቅሩን ሊጠብቁ ይገባል፤ መዋቅሩን ሳይከተሉና ከሚመለከተው አካል ጋራ ሳይመክሩ የሚሠሩት ሥራ ቤተ ክርስቲያኒቱን አደጋ ላይ የሚጥል ነው፤›› እንዳሏቸው ተመልክቷል፡፡
ዋና ሥራ አስኪያጁ ‹‹ውድቀት እንዳይደረስብዎ አማካሪዎችዎ ሊያዝንልዎ ይገባል፤›› ማለታቸውን የገለጹት የስብሰባው ተሳታፊዎች አያይዘውም ‹‹ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎቻቸው ክፋት ከዕድሜያቸው ዐሥር ዓመት አሳጥረዋል፤ እርስዎም በአማካሪዎችዎ የተነሣ ዕድሜዎ እንዳያጥር ያስቡበት፤›› ሲሉ መምከራቸውን ጠቅሰዋል፡፡
ውይይቱን በሰብሳቢነት የመሩት ፓትርያርኩ፤ ‹‹በሥራ ባለመታገዛቸውና ብቻቸውን በመኾናቸው›› ስብሰባውን ወደ ታች ወርደው ለመጥራት እንደተገደዱ አስረድተዋል፡፡ ፓትርያርኩ ባቀረቡት በጽሑፍ የተደገፈ ገለጻ÷ በቤተ ክህነቱ የመልካም አስተዳደር ዕጦቶች እንዳሉ፣ በሙሰኝነት፣ በዘረኝነትና በአድሏዊነት የሚገለጹ የብልሹ አሠራር ሒደቶች እንደሚታዩ ዘርዝረዋል፡፡
በቤተ ክርስቲያን ስም የሚደራጁ ማኅበራትና ግለሰቦች ሕግና ደንብ እየጣሱ መዋቅሯን እየተፈታተኗት እንዳለና ከመዋቅራዊ ቁጥጥር ውጭ የሚንቀሳቀስ ሀብትና ንብረት እያካበቱ በመኾኑ አካሔዳቸው ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ጥንካሬና ህልውና ፍጹም አደጋ እንደኾነ አብራርተዋል፡፡ መልካም አስተዳደርን ከማስፈን አንጻር ኹሉም የሥራ ሓላፊዎች ራሳቸውን በመፈተሽና በማጽዳት ችግሩን በዘላቂነት ለማስወገድ በሚደረግ ጥረት የድርሻቸውን እንዲወጡ አሳስበዋል፤ ያልተገባ ነው ያሉትን የማኅበራት አካሔድም ኹሉም ሊቃወመው ይገባል ብለዋል፡፡
ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ይወቁባቸው ስላሉት የአማካሪዎቻቸው ጉዳይም ‹‹አማካሪዎቼ ዓላማዬን የሚጋሩና የሚያስፈጽሙልኝ ሰዎች ናቸው፤›› ያሉት አቡነ ማቲያስ ‹‹አኹንም የምቀጥልበት መኾኑን አሳውቃለኹ፤›› ብለዋል፡፡
[በስብሰባው የተሳተፉት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአስተዳደር ዋና ክፍል ሓላፊ፣ ‹‹አንድ ጣታችንን ወደሌላው ስንጠቁም ሦስቱ ወደ እኛ እንደሚያመለክት አንዘንጋ፤›› በማለት ፓትርያርኩ ስለ ሙስናና ብልሹ አሠራር፣ ስለ ጎጠኝነትና ብኩንነት፣ ፍትሕን ስለማጉደልና ንጹሑን ሰው ስለመበደል፣ ስለ ትጋት ማነስና አባቶችን ስለ መከፋፈል፣ ለምእመናን መልካም አርኣያ ስላለመኾንና ለሀገር አለመቆርቆር ሌሎችን ሲገሥጹና ሲኰንኑ ስለራሳቸውና ስለከበቧቸው አማካሪዎቻቸውም እንዲያስቡበት አስታውሰዋቸዋል፡፡]
‹‹ብቻዬን ነኝ፤ በሥራም አልታገዝኹም›› ለሚለው የፓትርያርኩ ወቀሳ ‹‹ቅዱስነትዎ አዝዘው ምን ያልተፈጸመ ነገር አለ?›› በሚል ምላሽ የሰጡት ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ‹‹ያልተፈጸመ ነገር ካለ ለጉባኤው በይፋ ይገለጽ›› ሲሉ ጠይቀዋቸዋል፡፡ የመልካም አስተዳደር ችግርና የችግሩ መገለጫዎች በርግጥም እንዳሉ ያልሸሸጉት ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ መምሪያዎችና ድርጅቶች የበጀት ዓመቱን ዕቅድ በማውጣት፣ የክንውን ሪፖርት በአስተዳደር ጉባኤ በየወቅቱ እንዲያቀርቡ፣ ድክመቶች እንዲስተካከሉና ጠንካራ ጎኖች ታቅበው እንዲቀጥሉ መደረጉን በመግለጽ በፓትርያርኩ ጽሑፍ የቀረቡትን መረጃዎች ወቅታዊነት ሞግተዋል፡፡
በልማት ተግባራትና በሠራተኞች አያያዝ ባለፈው በጀት ዓመት የተፈጸሙ ተግባራትን የዘረዘሩት የጽ/ቤቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ዶ/ር አባ ኃይለ ማርያም መለሰ በበኩላቸው፤ በጥናት በተደገፉና ቀጣይነት ባላቸው የመልካም አስተዳደር ማሻሻያዎች የሚቀርቡ ቅሬታዎችና የተጉላሉ ባለጉዳዮች አለመኖራቸውን ገልጸዋል፡፡ ምክትል ሥራ አስኪያጁ አክለውም፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን የፋይናንስ ፖሊሲና የሒሳብ አያያዝ ሥርዐት ዘመናዊ ለማድረግ ዝግጅቱ መጠናቀቁን ጠቁመው ፓትርያርኩ በገለጻቸው የተጠቀሙባቸውን የችግር መግለጫዎችን አግባብነት እንደጠየቁ ታውቋል፡፡
መንግሥት የሲቪል ማኅበራትን የሚከታተለው ሕግ አውጥቶና ተቋም መሥርቶ መኾኑን፣ በሕጉ እገዛለኹ ያለ አብሮ እንደሚጓዝ፣ በሕጉ አልተዳደርም ያለ እንደሚወጣ የተናገሩት ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ቤተ ክርስቲያን ግን መንፈሳውያን ማኅበራት የሚቋቋሙበት ሕግ እንዳላወጣችና የምታቅፍበት መዋቅር እንዳልዘረጋች ገልጸዋል፡፡ በአገልግሎት ላይ ያሉትን መንፈሳውያን ማኅበራት በሕገ ወጥነትና በመዋቅር ባለመታዘዝ ለመጠየቅና ለመፈረጅ ሕጉን አውጥቶ በሥራ ላይ ማዋሉ መቅድም እንዳለበት በማስገንዘብ የፓትርያርኩን ግምገማና አፈራረጅ እንደተገዳደሩት ተጠቅሷል፡፡
[በተያያዘም የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊና ከቀንደኛ አማሳኞች ኃይሌ ኣብርሃና ዘካርያስ ሐዲስ ጋራ በመኾን ስብሰባዎቹን ያስተባበረው የመዝባሪዎች አለቃ ኤልያስ ኣብርሃ፣ ‹‹ማኅበሩ ለሕግ የማይገዛና የማይታዘዝ ነው፤›› እያለ ስሙን ለይቶ ሳይጠራ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የሰነዘረው ውንጀላ የብዙኃኑን የስብሰባውን ተሳታፊዎች ተቀባይነት እንዳላገኘ ተመልክቷል፡፡
በኹኔታው የተበሳጨው የሚ/ር ሺፈራው ቤተኛ ኤልያስ ኣብርሃ፣ ‹‹እንዴት ሕገ ወጥ አይደለም ትላላችኹ? አክራሪነትና ጽንፈኝነት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አለ የሚባለው ከማኅበሩ ጋራ በተያያዘ ነው፤›› የሚል በእብሪትና ተንኰል የተሞላ ክሡ የስብሰባው የጋራ የአቋም መግለጫ ኾኖ እንዲወጣ አካሉ እስኪንዘፈዘፍ እየተወራጨ ያደረገው መፍጨርጨር በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ የሰከነ ምከታና ማኅበሩ እንደ ቤተ ክርስቲያን ልጅነቱ በጥናት የታገዘ ምላሽ እንዲሰጠው በሚያሳስቡ የሥራ ባልደረቦቻቸው ጥረት እንዳልተሳካ ታውቋል፡፡]
በሌላ በኩል ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ፣ ‹‹ለኢትዮጵያ በረሓ ወርደው፣ ብረት አንሥተው የታገሉትና ዋጋ የከፈሉት ኹሉም ሕዝቦች ናቸው፤›› ብለው እንደተናገሩ የስብሰባው ተሳታፊዎች የጠቀሱ ሲኾን፣ ‹‹ሕገ መንግሥት ለኹሉም እኩል ነው፤ ለእገሌ ሚኒስትር እናገራለኹ፤ ለእገሌ ደኅንነት እደውላለኹ እያሉ አያስፈራሩን፤›› በማለት ፓትርያርኩን እንዳሳሰቧቸውም ሳይጠቅሱ አላለፉም፡፡
‹‹የመልካም አስተዳደርን አስተሳሰብ ማበልጸግ›› በሚል ርእስ በፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት ትእዛዝ በአ/አ ሀ/ስብከት የተጠራው ስብሰባ በርግጥም ስለ ርእሱ የተደረገ ሳይኾን በማኅበረ ቅዱሳንና በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ላይ ያነጣጠረ እንደነበር ቀንደኛው አማሳኝ ኃይሌ ኣብርሃ ቀድመው የተመረጡ ሰዎች ብቻ እንዲናገሩ በተፈቀደው ‘ውይይት’ ላይ ግልጽ አድርጓል፡፡ የስብሰባው እውነተኛ ዓላማ ደግሞ፣ ለሚመለከተው መንግሥታዊ አካል በይፋ ተነግሯል ከተባለው በተፃራሪ በማኅበረ ቅዱሳን ላይ ቅስቀሳ በማካሔድ ፓትርያርኩ በማኅበሩ ላይ የያዙት ውድቅ የተደረገ አቋም በቅዱስ ሲኖዶሱ ተቀባይነት እንዲያገኝ ጫና ለመፍጠር አልያም ለኃይል ርምጃ ለማመቻቸት የታቀደበት እንደነበር ‘ንቡረ እድ’ ኤልያስ ኣብርሃ በመንበረ ፓትርያርኩ በተካሔደው ስብሰባ ባራመደው አቋም ግልጽ አድርጓል፡፡ (ፎቶ: አ/አበባ ሀ/ስብከት)
አቡነ ማትያስ በዚኹ ሳምንት ማክሰኞ፣ ከቋሚ ሲኖዶሱ ጋራ ሳይመክሩ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአድባራትና ገዳማት አለቆችና ጸሐፊዎች ጋራ ባደረጉት ስብሰባ፣ ማኅበረ ቅዱሳንን ከብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ ጋራ ደርበው በሚወነጅሉ አንዳንድ አማሳኝ አስተዳዳሪዎችና ጸሐፊዎች ብፁዓን አባቶችን ማዘለፋቸውን የጠቀሱት አቡነ ማቴዎስ፣ በዚኽም ኹሉም አባቶች ቅሬታ እንደተሰማቸውና እንዳዘኑባቸው በግልጽ ነግረዋቸዋል፡፡
ፓትርያርኩ ዓመቱን በሙሉ በየደረጃው እቀጥልበታለኹ ባሉት ስብሰባ÷ አጀንዳዎች መዋቅር ሳይጠብቁ፣ ጥናት ሳይደረግባቸውና ሳይብላሉ ውይይቱ ለሚዲያዎች ዘገባ ክፍት መደረጉ ቤተ ክርስቲያኒቷን ለአላስፈላጊ የውጭ ተጽዕኖና ለአጉል ትችት እንደሚያጋልጣት በተሳታፊዎች አስተያየት ተተችቷል፡፡
* * *
(ምንጭ፡- አዲስ አድማስ፤ ቅፅ ፲፫ ቁጥር ፯፻፷፱፤ ጥቅምት ፩ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም.)

አቡነ ማቴዎስ ፓትርያርኩን ተቃወሙ፤ “አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎች ክፋት ዕድሜያቸውን አሳጥረዋል፤ ቅዱስነትዎም ያስቡበት” አሏቸው | Zehabesha Amharic

አቡነ ማቴዎስ ፓትርያርኩን ተቃወሙ፤ “አቡነ ጳውሎስ በአማካሪዎች ክፋት ዕድሜያቸውን አሳጥረዋል፤ ቅዱስነትዎም ያስቡበት” አሏቸው | Zehabesha Amharic
This is what the TpLf kemalams are doing on innocent civilians. Their hate crime is beyond your imagination. Hmmm this is just hard to explain, I am really sad and angry. God is watching you, say or do something to stop the current racist (ethnic supremacist) regime for those of you supporting because of whatever reason. God will pay you back one way or another and I personally make sure justice is served no matter how long it will be taking as long as I am alive.

Friday, 10 October 2014

ኢትዮጵያ ከመከላከያ ኢንዱስትሪና ከኃይል ማመንጨት ውጪ ያሉ ዘርፎችን ክፍት እንድታደርግ አይኤምኤፍ አሳሰበ
በቅርብ ዓመታት የገንዘብ እጥረት ይገጥማታል አለ
-ኢትዮጵያ ለዓለም አቀፍ ገበያ ቦንድ ልትሸጥ ነው
የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ሲገመግም የቆየው የዓለም ገንዘብ ድርጅት (አይኤምኤፍ) የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ቡድን ሰሞኑን ይፋ ባደረገው ሪፖርት፣ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን ለግሉ ዘርፍና ለውጭ ባለሀብቶች ብትከፍት አሁን ካለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት የበለጠ ተጠቃሚ እንደምትሆን አስታወቀ፡፡
የግምገማውን ይፋዊ ሪፖርት ያወጣው አይኤምኤፍ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት ዘርፍንና የመከላከያ ኢንዱስትሪን ለጊዜው በመያዝ፣ ሌሎቹን የኢኮኖሚ ዘርፎች ክፍት ብታደርግ ተጠቃሚ ትሆናለች የሚል ምክረ ሐሳብ ሰጥቷል፡፡
አይኤምኤፍ ከዚህ ቀደም የቴሌኮሙዩኒኬሽንና የባንክ ዘርፍ ነፃ እንዲሆን በተደጋጋሚ የጠየቀ ቢሆንም፣ በአሁኑ ሪፖርቱ ግን ተጨማሪ ዘርፎችንም አካቷል፡፡ የትራንስፖርት፣ የሎጂስቲክስ፣ የስኳር ዘርፎች ለግል ባለሀብቶችና ለውጭ ኢንቨስተሮች ክፍት እንዲሆኑ ጠይቋል፡፡ ይህ ተግባራዊ ቢሆን አገሪቱ በአገልግሎት አሰጣጥ፣ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማስገባትና የአገር ውስጥ አቅምና ጥረትን በማጎልበት ረገድ ተጠቃሚ እንደምትሆን አስረድቷል፡፡
የአይኤምኤፍ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ቡድን በኢትዮጵያ ቆይታው የአገሪቱ ኢኮኖሚ ወደፊትም በጥንካሬው የሚቀጥል ቢሆንም፣ የተለያዩ ፈታኝ ሁኔታዎች እንደሚገጥሙት ባወጣው ሪፖርት ይገልጻል፡፡ ከእነዚህም መካከል ለከፍተኛ የመንግሥት ፕሮጀክቶች የሚውል የገንዘብ እጥረት እንደሚገጥመው፣ በዓለም አቀፍ የገበያ አለመረጋጋቶች በሚፈጥሩት የዋጋ መቀነስ ምክንያት የውጭ ምንዛሪ እጥረት ሊገጥም እንደሚችልና ከአየር ንብረት ለውጥ ጋር የተያያዘ ድርቅ ሊከሰት እንደሚችል አትቷል፡፡
ከፍተኛ የመንግሥት ፕሮጀክቶች የፋይናንስ እጥረት ሊገጥማቸው ይችላል ካለባቸው ምክንያቶች አንዱ፣ እንደ ኢትዮ ቴሌኮምና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ያሉ የመንግሥት የመሠረተ ልማት ተቋማት በራሳቸው እያገኙት ያለው የአገር ውስጥና የውጭ ብድር የሚፈጥረው ጫና ነው፡፡
ለአብነት ያህል የኢትዮጵያ ምድር ባቡር ኮርፖሬሽን ከሁለት የቻይናና የቱርክ ኩባንያዎች ጋር የ3.9 ቢሊዮን ዶላር የፕሮጀክት ስምምነት መፈራረሙን፣ በተመሳሳይም ኢትዮ ቴሌኮም 1.6 ቢሊዮን ዶላር የፕሮጀክት ስምምነት ከቻይና ቴሌኮም ኩባንያዎች ጋር መፈራረሙን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ እነዚህና ሌሎች የመሠረተ ልማት ተቋሞች በብድር ለኢንቨስትመንት የሚያወጡት ከፍተኛ ገንዘብን መንግሥት እንደ ራሱ የውጭ ዕዳ ቆጥሮ መከታተል ካልተቻለ፣ በማክሮ ኢኮኖሚው ላይ የሚፈጥረውን ተፅዕኖ መገንዘብ ያስቸግራል ሲል አሳስቧል፡፡
ከአይኤምኤፍ ቡድን አባላት ጋር የተወያዩት የመንግሥት ባለሥልጣናት ከግብርና ኢኮኖሚ ወደ ኢንዱስትሪ የሚደረገው ሽግግር ፍጥነት አዝጋሚነቱ ላይ መግባባታቸውን፣ ይህንን ለመቀየርም በመሠረተ ልማት ዝርጋታ ላይ ትኩረት በማድረግ ምቹ ሁኔታን እንደሚፈጥሩ መግለጻቸውን ሪፖርቱ ያትታል፡፡
በተጨማሪም የግሉ ዘርፍ በሚኖረው ኢኮሚያዊ ሚና ላይ መግባባታቸውን፣ በተለይም ስትራቴጂካዊ ከሚባሉት ዘርፎች ውጪ ያሉትን ዘርፎች ለግሉ ዘርፍ ክፍት ለማድረግ እየሠሩ መሆናቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡
ይሁን እንጂ በመንግሥት የመሠረተ ልማት ተቋማት የአገር ውስጥና የውጭ ብድር ክምችት በሚፈጥረው ተፅዕኖ ላይ መግባባት አለመቻላቸውን ሪፖርቱ ይጠቁማል፡፡ እነዚህ ተቋማት ለሚያገኙት ብድር የኢትዮጵያ መንግሥት ዋስትና እንዳልሰጠና ተቋማቱ እንደ ንግድ ድርጅት በማትረፍ ላይ ተመሥረተው የሚሠሩ በመሆናቸው፣ በራሳቸው ዕዳውን እንደሚከፍሉና እንደ መንግሥት ዕዳ ሊታይ አይገባውም የሚል ክርክር በኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት አማካይነት መቅረቡን ሪፖርቱ ይገልጻል፡፡
ነገር ግን የእነዚህ ተቋማት አጠቃላይ ሀብትና ዕዳን የሚቆጣጠር ኤጀንሲ ለማቋቋም መስማማታቸውን፣ እንዲሁም እንደ ኢትዮ ቴሌኮም ያሉ አትራፊ የመንግሥት ተቋማት ዓመታዊ የኦዲት ሪፖርት ለመንግሥት እንዲያቀርቡ መስማማታቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡
በተያያዘ ዜና አሁን ያለው የመንግሥትም ሆነ የመንግሥት ተቋማት የአገር ውስጥና የውጭ ብድር ክምችት ተፅዕኖ እንደማያመጣ የሚገልጸው መንግሥት፣ ዓለም አቀፍ ቦንድ (ሶቨሪን ቦንድ) ለመሸጥ መዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል፡፡ መንግሥት ውሳኔውን የወሰነው የአገሪቱን የፋይናንስ ምንጭ ለማስፋፋትና አገሪቱ እምነት የሚጣልባት መሆኑን በመግለጽ የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ በማቀድ መሆኑን፣ የገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስትሩ አቶ ሱፍያን አህመድ ባለፈው ቅዳሜ በሰጡት መግለጫ ተናግረዋል፡፡
በአሁኑ ወቅትም ከሁለት የውጭ ባንኮች ጋር ድርድር እየተደረገ መሆኑንና እስከ ታኅሳስ ወር ድረስ እንደሚጠናቀቅ ገልጸዋል፡፡ አቶ ሱፍያን እንደሚሉት የመንግሥትን ሉዓላዊ ቦንድ ለዓለም አቀፍ ገበያው በማቅረብ የሚገኘው ብድር ለመሠረተ ልማት ዝርጋታ ይውላል፡፡ ይሁን እንጂ ለየትኞቹ የመሠረተ ልማት ዘርፎች እንደሚውል አልገለጹም፡፡
መንግሥት ወደ ዓለም አቀፍ የቦንድ ገበያው ለመግባት የወሰነው በሦስት ታዋቂ ዓለም አቀፍ ተቋማት የአገሪቱ ብድር የመሸከምና የመክፈል ደረጃ ተመዝኖ በአማካይ የ‹‹B›› ደረጃ ከተሰጠው በኋላ ነው፡፡ ላለፉት በርካታ ዓመታት መንግሥት በሁለትዮሽ ድርድር ሲያገኝ ከነበረው የአገሮች ብድር በመውጣት ተጨማሪ አማራጮችን እየፈለገ ይገኛል፡፡ ከላይ ከተገለጸው ዓለም አቀፍ የቦንድ ሽያጭ በተጨማሪ የፖታሽ ማዕድን እምቅ ሀብቱን በዋስትና በማስያዝ የመበደር እንቅስቃሴ ውስጥ መግባቱን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

Amb. Girma Birru and Solomon Tadesse: Two Sides of a Coin

October 10, 2014
by Mihret Feleke
This article is made possible after I heard the interviews given by the EPRDF Ambassador to the US Girma Birru who defended the actions and acclaimed the actions of his embassy staff Solomon Tadesse who shot fired at unarmed protestors in broad day light outside the embassy premises. I am not writing this article to dwell on what happened and deal with what should have been done. Rather, I was deeply ashamed by the Ambassadors repeated and relentless argument in the interview he gave afterwards that regarded the action of the gunman as proper and right while to the mind of all sane people it is none but an outrageous and illegal act never seen in the real world before. What troubles me most with the Ambassadors determination of defending the act is that if he and the TPLF regime believe it is an act of patriotism than a breach of the law and order of the host nation we have no guarantee that this same action will not be repeated again and Ethiopians would not be subjected to similar horrific event. For that, I believe, the Ambassador has to be required to recant his words out of decency to the host nation as well as those Ethiopians who came close to be killed by the gunman.
I was deeply ashamed by the Ambassadors repeated and relentless argument
Girma Birru
Solomon Tadesse who had been posted at the Ethiopian embassy in Washington and fired shots on unarmed protestors had departed from the US to avoid persecution under US laws for the crimes he committed. In addition, we also have learned that the US authorities have issued an arrest warrant for his apprehension when ever and where ever he is captured unless protected by the diplomatic immunity under the Vienna convention, which bestows protection to diplomats of a given nation from being subjects under the laws of a host nation. His case being a pending case that would be pursued when the time comes the post incidence stance taken by the Ambassador has to be the focus and scrutiny of law enforcement agencies as well as other US authorities and Human Rights groups.
The interviews the Ambassador gave to Medias here in the US and back home in Ethiopia is troubling to all rational and law-abiding people who adhere to the principles of the rule of law. On all of the interviews the Ambassador gave, he had not taken responsibility nor admits the action taken by the agent in the embassy as a wrongful act. He rather came out with a determined stance to defend the actions of the agent by saying ‘he has done a right job’ for firing a deadly weapon on unarmed protestors outside of the embassy compound. It is this stance taken by the Ambassador that is equally outrageous as the actions of the agent himself that I made the decision to deal with it in this article and point out the basis that would justify my call for investigation in to the role of the Ambassador to this outrageous act that put the lives of civilians in grave danger and would give a confidence to other incoming agents to commit such acts using their diplomatic immunity.
The US law enforcement agencies of course know a lot about criminal acts and how the law is used so as to incriminate those who break it. In addition, the way the gunman’s case has been handled had been appreciated by so many Ethiopians residing in the US. However, beyond taking the action on the perpetrators the US authorities have to question the open and unambiguous stance taken and conviction held by the Ambassador that undermines the laws and orders of this great nation by implicitly suggesting the action taken by the US authorities is wrong while defending and showing his support to the action of the agent. It is true that although crimes committed by anyone would directly make that person the principal subject to the actions taken it also look in to accomplices and collaborators who have allowed themselves to propagate, defend and congratulate the actions committed breaking the laws of this nation. So as to please the TPLF masters back home and calm their anger caused by the departure of one of their own the Ambassador has chosen to disrespect and undermine the law and order the US.
However, the Ambassador’s relentless defense of the agent calling his actions that could well be considered as serious as ‘attempted murder’ right and proper while obviously the reality is otherwise is a typical example that shows how the system of the TPLF led government works in Ethiopia as well as where ever their agents reside. And considering this incident as an isolated event would also be wrong since such acts are committed by the TPLF regime anywhere and anytime on those who call for the end to its narrow ethnic based politics and the hegemony of a minority group as well as the draconian press law, anti-terrorism and NGO and CSO laws. The actions of Mr. Solomon and the defense of the Ambassador is a microcosm of the general reality in Ethiopia that Ethiopians subjected to day in and day out under the TPLF rule.
The TPLF government that has been in power for more than three decades still engages in practices that can be considered un-characteristic of a government and still has the attributes of a rebel group with characteristics of a terrorist group. We have learned before from the US embassy in Addis Ababa diplomatic message surfaced by Asange that the TPLF government plants explosives, where civilians live, and kill citizens so as to blame killings on opposition groups and meet its political agenda to legitimize its criminal acts committed against opposition groups. The explosions in Addis Ababa and other places in Ethiopia a couple of years ago were the acts of the government itself so as to blackmail the Oromo Liberation Front and use it as an excuse to jail, torture and kill its members. And if the TPLF regime claim that Ginbot 7 planted explosive to kill civilians we all have to first say lets first start the investigation from TPLF itself since it is in its nature to act as one than a responsible government of the people.
Unlike what is in the attributes of any government in the world that work for unity and co-existence, the TPLF government deliberately propagates ideas that widen gaps between different groups creates hatred and animosity so as to protect it minority hegemony and power used as a means of protecting the economic interest of its members as well as its ethnically connected cronies. It is indeed unprecedented and unheard of in any place in the world but in Ethiopia a population that accounts for six percent of the total population controls ninety percent of the nation’s security, police and military high rank positions as well as other federal institutions. In order to sustain such a status-quo the TPLF regime engages itself in any form of action including those adopted by terrorist organizations.
On the interview he gave, the accusation of those unarmed protestors by the Ambassador that his embassy staff member shot a gun on their face as members of terrorist organizations like Oromo Liberation Front and Ginbot 7 is indeed shameful and despicable. This is a usual game TPLF has mastered on which is a deceptive maneuver meant to shift the blame. However, this incident cannot be hidden nor denied since it is committed on broad day light while the whole world is watching. When I say this I am very convinced that let alone in the US, even in Ethiopia no Ethiopian opposition party has ever shot a gun or killed a single civilian to advance its political agenda. No international or regional actors and groups has ever charge no such group committing such crime. The atrocities committed by OLF on ethnic Amharas during the outset of TPLF rule was in fact committed with TPLF being the accomplice than an action committed on its own. But the world knows and Ethiopians have lived it for more than two decades that if there is any group that used violence as a means of advancing political agenda and protect absolute monopoly of power, it is TPLF that has jailed, killed and tortured thousands of civilians and it is still carrying out such acts wherever the oppressive hands of the regime reaches out to.
Keeping aside the regimes two decades old record of killing and torturing as means of running its political agenda the recent shooting by one of the cadre agent of the TPLF regime in the US capital speaks the general fact who have the tendency to engage in acts considered to have terrorist nature. Since the basic underpinning objective of a terrorist group is advancing its narrow and extremist agenda through the use of violence with no regard to civilian life and safety that it exactly what we have seen in TPLF today and yesterday. And if there is any group that should be labeled as a terrorist group it would be no one but the TPLF elites and rank and file in Addis Ababa and every where its agents are working as ‘diplomats’. Although I know the international community fully realizes this undeniable fact I just wanted to reiterate the fact as a way of awakening their conscious so as to invigorate their action in pressuring the regime in Ethiopia to come to its senses and be party of sanity and join the civility and rationality people of the 21st century has embarked on.
The TPLF regime that has itself been terrorizing the nation with no regard to its own constitution and respect to international laws of human rights labeling different peaceful oppositions, free journalists, activists and bloggers as terrorists is a mockery of the highest order. In TPLF controlled Ethiopia demanding human and democratic rights, treatment of all ethnic groups as equal and the demand for the rule of law are considered an act of terrorism that would subject one to be jailed, tortured and killed while TPLF itself being the legislature, police, prosecutor and judge. So many Ethiopians of different walks of life have been slaughtered on the basis of the ‘anti-terrorism’ law and thousands are languishing in Ethiopian prisons as I speak. The belligerent TPLF regime in Ethiopia, however, that does not budge to the call of United Nations, Human Rights Watch, Amnesty International as well as US government and European Union request to stop using the law as a tactic used to advance political agendas has continued to target Ethiopians on such phony accusations leading thousands to exile for fear of their life.
Therefore, while summing up my thoughts, I would say that as one of the exiled Ethiopians living in the US, I deeply believe the US government would conduct a thorough background investigation in to the people the TPLF government send as diplomats to its embassies. Because, as we have learnt since some years back the TPLF regime has made it a policy to staff all government positions with cadres than professionals. So, the attributes of the regime that reflects violence and cruel treatment as an instrument of protecting power that is used to advance the economic interest of its members and affiliates would be carried to anywhere its agents are sent. The actions of Solomon Tadesse last week and the determination of Amb. Girma Birru defending the action as proper and right by disrespecting US law and its enforcement agencies actions and decisions is a good example. We Ethiopians, who reside in the US who enjoys the freedom and rights this greate nation enshrined to all people who set foot on its soil plead to the US authorities to protect our safety and security from the regime that exiled us in the first place and attempt to extend its hands here in the land of the free and attempt to suppress our voice by the use of a gun.
Thank you
Thank you America!
/Menelik the Diplomat/
The well mannered personality and friendly spirit of Emperor Menelik was the one that attracted a massive number of traders and investors from a distant lands to flood toward our offshore in that far way generation and even though he was a man of a few words, however Menelik was compassionate to the extreme and that is why the nation named him "Emeye Menelik".
Here in this image, Emperor Menelik is seen welcoming an Armenian guest named Krikorios Boghossian and even though the time is undated, but I am assumed that this historical visit must have taken place after the battle of Adwa, because that is when the historical announcement of Emperor Menelik, calling the westerners to come to our land to invest, to work to teach and to live peacefully was announced.
Emperor Menelik loved people, he was all about country and he was a leader who taught his people courage, bravery, confident and that is why soon after the battle of Adwa, a certain British News journal wrote and glorified him by saying “Menelik destroyed Italy”
Not only that, The graceful Menelik had also triggered a lasting fear and doubt in the mind of the whole Europeans and saved Ethiopia from the coming colonization.

Thursday, 9 October 2014

ሰለሞን ተካልኝ ማነው ? በተገኘበት ራሱን ከንቱ ያደረገ ወላዋይ (አቋም የሌለው ሰው) ፡ Who is Solomon ...

'ባንዲራችንን አትድፈሩት እኛ እንድፈረው''፤
ከትላንት በስትያ እኛ ሀገር ሰላም ብለን ትምህርታችን ላይ አንገታችንን ደፍተን በነበረበት ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ ከሁለት ወገን በሆነ ሰላማዊ ሰልፍ ኢትዮጵያውያን ተፋጠው ነበር።
በዚህ ወገን ያሉት ኢትዮጵያውያን ባለፈው ጊዜ ከኛ በላይ ተኳሽ ላሳር ያለውን የደደቢት ጓድ አሜሪካ ''ኪቻ'' ብላ ስላባረረችው ገለታ ለማለት የተገኙ ሲሆን፤
በሰለሞን ተካ የተመራው የመንግስት ከንፈር ወዳጅ ሰልፈኞች ደግሞ (በቅንፍም፤ እነዚህን ሰልፈኞች ከምንላቸው ሰይፈኞች ብንላቸው ይሻላል መሰል) እና እነርሱ በሌላ በኩል ''ወዲ ወይኒ እንኳንም ተኮሰ'' እንደውም የጥይት ጩህት ናፍቆን ነበር ብለው ሊመሰክሩ ሰልፍ ወጥተው ነበር።
ከዚህ በተጨማሪ በሰልፉ ላይ የተገኙት እንዚህ የኢህአዴግ ብልግና ደጋፊዎች ''ባንዲራችንን አትድፈሩት እኛው እንደፍረዋለን'' ሲሉ ልክ አቶ መለስ ዜናዊ የደፈሩት አይነት አደፋፈር ባንዲራው ላይ ፈጽመዋል።
እኛም በሩቁ ነገሩን የተመለከትን ሰዎች ባንዲራ የምትገለብጪ ወዮልሽ ....ትገለበጫለሽ... ወዮልሽ!!! ስንል ለትዕቢተኞቹ ትንቢት ተናገረናል!
የVOA ጋዜጠኞች ቅሌት ዛሬም ቀጥሏል
VOA ማክሰኞ በቦታው ተገኘሁ ብሎ የሰልፈኞቹን ብዛት በተዛባ ሁነታና በቅጥፈት 15ና 20 ናቸው ብሎ ተናግሮ ሲያበቃ፤ ዛሬም ወያኔን ለመጥቀም መረጃ ማዛባቱን ቀጥሎበት ለአድማጭ ያልተረጋገጠ፣ ለማያውቁ የዋሆች ክርክር ውስጥ የሚያስገባና፣ የበረራ ቲኬት ተገዝቶላቸው በመከራ ከየ እስቴቱ መጥተው በመዋጮ የተሰባሰቡትን ሆዳሞች ተጨምረውበት እንኳን እጅግ አናሳ የነበሩትን የወያኔ ደጋፊዎችን በማምታታት አብዝቶ ለማሳየት፤ ከጋዜጠኛ የማይጠበቅ እጅግ የወረደ ዘገባ አቅርቧል።
እንደው እስኪ ፍረዱ ሰልፉ ከተጠናቀቀ ከ24 ሰአታት በላይ ካለፉ በሗላ ጠይቆ የተሰላፊዎቹን ተወካዮች ለአድማጭ አሃዞችን እንደ እውነት ማቅረብ ምን ይባላል!? ወያኔ ተዋሸለትም፣ ተደበቀለትም፤ ከህዝብ ትከሻ ላይ አሽቀንጥረን የምንጥልበት ጊዜው በጣም ቀርቧል። ለነገሩ ለተከፈለው ገንዘብ ብሎ የተጠራቀመ፤ የገዛ ባንዲራውን እንኳን የማይለይ ሆዳም ቢሰባሰብ ምን ይፈይዳል!? “ሺሺሺ… አንድ ጎማ አይነፋም” ይሉ የለ… !

Wednesday, 8 October 2014

በኢትዮጵያ ኢምባሲ ተኩስ የከፈቱት ዲፕሎማት ላይ የእስር ማዘዣ ወጣ
ባለፈው ሰኞለት በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ለተቃውሞና ለአቤቱታ የተሰባሰቡ ሰዎች ላይ ሽጉጥ በመምዘዝ የተኮሰው የኢምባሲ የጥበቃና ደህንነት ክፍል ሰራተኛ፤ የዩናይትድ ስቴይትስ አቃቢ ህግ ቢሮ እስከ 30 ዓመት በሚያስቀጣ ወንጀል ክስ ከፍርድ ቤት እስር ማዘዥ እንደተሰጠው አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኢምባሲ ጥበቃና ደህንነት አታሼ የ46 ዓመቱ አቶ ሶሎሞን ታደሰ ገ/ስላሴ የተከሰሱበትና የእስር ማዘዣ የወጡበት ህግ “ለመግደል በማሰብ ጥቃት ማድረስ” የሚል ነው። የወንጀል ደረጃውም እስከ 30ዓመት የሚደርስ ከፍተኛ ቅጣት የሚጣልበት እንደሆነ በዩናይትድ ስቴይትስ አቃቢ ህግ ቢሮ የዋሽንግተን ዲሲ ቅርንጫፍ ቃል አቀባይ ዊሊያም ሚለር ለቪኦኤ በጽሁፍ ገልጸዋል። ሰኞ መስከረም 19 ቀን በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኢምባሲ ለተቃውሞ ሰልፍና ለአቤቱታ የወጡ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ወደ ኢምባሲው ቅጥር ግቢ ከገቡ በኋላ በተፈጠረ ሁኔታ አቶ ሰሎሞን ተኩስ ከፍቷል። በዚህ የወንጀል ምርመራ፤ የዝግጅት ክፍላችን ከዚህ ቀደም ለፍትህ ምንስቴርና ለውጭ ጉዳይ ምንስቴር ባቀረበው ጥያቄ፤ የምርመራው አትኩሮት በተኳሹ ላይ ብቻ ያነጣጠረ ነው? ለሚለው ጥያቄ የዲሲ አቃቢ ህግ ቢሮ ሲመልስ ዝርዝሩ የሲክሬት ሰርቪስ ቢሆንም “በዚህ ክስተት ላይ ሌላ ክስ የቀረበበት ሰው የለም” ብለዋል።
http://amharic.voanews.com/