የታሰሩ ዜጎች አሸባሪዎች ስለነበሩ አልነበረም፡፡የፖለቲካ ጨዋታው ሌላ በመሆኑ ምክንያት የዚህን ሁሉ ህዝብና ባለሙያ ጩኽት ኢህአዴግ ከምንም ሳይቆጥር የዚህን አዋጅ ወደ ሚሞግቱት ፊቱን በማዞር ሲቃወሙ የነበሩ ግለሰቦችንና ተቋማት ላይ በጠራራ ጸሀይ የወሰደው እርምጃ በእርግጥም ትክክል እንደነበሩ አረጋግጧል፡፡የፀረሽብር አዋጁ በፀደቀ ማግስት የያኔው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ የመንግስታቸውን ሪፖርት ለማቅረብ ፓርላማ ተገኝተው ስለአዋጁ ካብራሩ በኋላ ከምክር ቤቱ ለቀረበላቸው ጥያቄ መልስን ሰጥተው እብዳጠናቀቁ ለአንድነት ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች ‹‹ዋ ዋጋ ትከፍላላችሁ በማለት በፓርቲው አመራርና አባላት ላይ ሽብር አወጁ ››ያኔ ይህንን ማስፈራሪያቸውን በቃላት ብቻ ገድበውት አላለፉም፡፡አንዴ ሰይፋቸውን መዘዋልና ፓርተአቸው አስቀድሞ ጣት የቀሰረባቸውን እስር ቂምና ቁርሾ የተያዘባቸው በርካታ ትንታግ ፖለቲከኞችን፤ጋዜጠኞችን ለሀገራቸው ተስፋን የሰነቁ ኮኮብ ልጆችን በአዋጁ ጎራዴ ሰየፉት ፡፡ከእነዚህ ሰለባዎች ውስጥ በትህትናው ፡በፀባዩና በምግባሩ እንዲሁም በአካዳሚክ እውቀቱ የሚታወቀው ወጣቱ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አንዷለም አራጌ ፤የአንድነት ፓርቲ የብሔራዊ ምክር ቤት አባል ወጣቱ ፖለቲከኛ ናትናኤል መኮንን፤መምህር አሳምነው ብርሀኑ፤አንጋፋው የፕሬስ ተሟጋችና አለማቀፍ የፖለቲካ ተንታኝ ጎልማሳው እስክንድር ነጋ ፤የኦፌዴን ምክትል ለቀመንበርና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መምህር በቀለ ገርና የኦህኮ አመራር አባል የነበሩት አቶ ኦልባና ሌሊሳን እነደምሳሌ መጥቀስ የሚቻሉ የፀረሽብር አዋጁ ሰለባዎች ናቸው፡፡
No comments:
Post a Comment