Monday, 10 March 2014

የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን መሰጠቱ ተረጋገጠ
======================

የአፄ ዮሃንስ IV በመተማ የተሰውበት 125ኛ ዓመት ትናንት እሁድ የካቲት 30 ተዘክሮ ዉሏል። አፄ ዮሃንስ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለማስከበር ሲሉ መስዋእት የሆኑበት መተማ አሁን በህወሓቶች ለሱዳኖች (ለድርቡሽ) በሚስጢር ተሰጥቷል። የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን መሰጠቱ በማስረጃ አረጋግጠናል። በኢትዮ-ሱዳን ድንበር አከባቢ የነበሩ የኢትዮጵያ አርሶአደሮች መሬታቸው ለሱዳን ተላልፎ በመሰጠቱ ምክንያት የኢትዮጵያ መንግስት ሌላ ተለዋጭ መሬት የሰጣቸው ገበሬዎች በአካል አግኝቼ አነጋግርያቸዋለሁ። በጣም ብዙ አርሶአደሮች ተለዋጭ መሬት እንደተሰጣቸው አብራርተው የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን ተሰጥቷል የሚባለውም ትክክል መሆኑ መስክረዋል።
...
ይገርማል። አንዳንዱ መሬቱ አሳልፎ ላለመስጠት ይሰዋል። ሌላ ደግሞ የሀገር መሬት በአሮጌ አውሮፕላን ይለውጣል፣ ይሸጣል። ወይ ህወሓቶች! የኢትዮጵያን መሬት እየቆረሱ ለመቸብቸብ ነው እንዴ ስልጣን የያዙ?
በቃ የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን መሰጠቱ ተረጋግጧል። ዉሳኔው ሕገወጥና ተቀባይነት የሌለው ነው። መሬታችንን እናስመልሳለን።

No comments:

Post a Comment