Tuesday, 21 July 2015

የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አስመራ መግባት በሰራዊቱ ውስጥ ትልቅ መነቃቃት ፈጥሯል

የፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አስመራ መግባት በሰራዊቱ ውስጥ ትልቅ መነቃቃት ፈጥሯል


የአርበኞች ግንቦት7 ሊቀመንበር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ “ለነጻነት፣ ለፍትህና ለዲሞክራሲ የሚደረገውን ትግል መሬት ላይ ወርዶ መምራት ይገባል” በሚል እምነት በከፍተኛ ውጣ ውረድ ከአሜሪካ ኤርትራ መግባታቸው እንደተሰማ በአርበኞች ግንቦት7 ሰራዊት ውስጥ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ፣ አስመራ በሚገኘው የድርጅቱ ጽህፈት ቤት አቀባበል ያደረጉላቸው ሻለቃ አክሊሉ መዘነ ተናግረዋል።በዋና ጽህፈት ቤቱ የሚሰሩ የፖለቲካ እና የውጭ ግንኙነት ክፍል አባላት ለፕሮፌሰሩ በጋራ አቀባበል እንዳደረጉላቸው የገለጸው ሻለቃ አክሊሉ፣ ከአባላት ጋር ውይይት ማድረጋቸውን ገልጸዋል።
በሰራዊቱ ውስጥ የታየው መነቃቃት ለነጻነት የሚደረገው ትግል እንዲፋጠን፣ በተለይም ከተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር የሚደረገውን ተቀራርቦ የመስራት ድርድር እንዲፋጠን እንደሚያደርገው ሳለቃ አክሊሉ ተስፋቸውን ገልጸዋል።
ፕ/ር ብርሃኑ አስመራ አየር ማረፊያ ሲደርሱ ከፍተኛ የኤርትራ ባለስልጣናት ተቀብለዋቸዋል።የፕ/ር ብርሃኑ አስመራ መድረስ ዜና ይፋ ከሆነ ጀምሮ፣ በአገር ውስጥ ከፍተኛ መነቃቃት መፈጠሩን ኢሳት ከተለያዩ አካባቢዎች የሚደርሱት መረጃዎች ያመለክታሉ። አርበኞች ግንቦት7ትን ለመቀላቀል የሚጠይቀው ህዝብ እየጨመረ መምጣቱንም ከድርጅቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ፕ/ር ብርሃኑ ግንቦት7ትን በሊቀመንበርነት ሲመሩ ቆይተው ፣ አርበኞች ግንቦት7 ውህደት ከፈጸሙ በሁዋላ የውህዱ ድርጅት ሊቀመንበር ሆነዋል። በውህደቱ ላይ ለመገኘት የነበራቸው ውጥን ከጉዞ ሰነድ ጋር በተያያዘ ባለመሳካቱ፣ ለመሪነት የተመረጡት በሌሉበት ነው። ይሁን እንጅ በውህደቱ ወቅት ለጉባኤተኛው በስልክ ባስተላለፉት መልክት፣ አንዳንድ ችግሮች ተፈተው በቅርቡ በረሃ ወርደው እንደሚቀላቀሉዋቸው ቃል ገብተው ነበር።
በምርጫ 97 በተደረገው ምርጫ አሸንፈው የአዲስ አበባ ከንቲባ ሆነው የተመረጡት ዶ/ር ብርሃኑ፣ ምርጫውን ተከትሎ በተፈጠረው ውዝግብ ከሁለት አመት ላለነሰ ጊዜ በእስር ቤት አሳልፈዋል። ከዚያም አሜሪካ በሚገኘው በክኔል ዩኒቨርስቲ በመምህርነት ሲያገለግሉ ቆይተው ከወራት በፊት የሙሉ ፕሮፌሰርነት ማእረግ አግኝተዋል።

Thursday, 16 July 2015

ስዊድን፥ ጠቅላይ ሚንስትር ከኢትዮጵያ መልስ ሆስፒታል ገቡ

ስዊድን፥ ጠቅላይ ሚንስትር ከኢትዮጵያ መልስ ሆስፒታል ገቡ
የስዊድኑ ጠቅላይ ሚንሥትር ሽቴፋን ሎፍቨን ከኢትዮጵያ ወደ ስዊድን በመብረር ላይ ሳሉ ስለታመሙ ሀገራቸው ሲደርሱ ሐኪም ቤት መግባታቸውን የሚንሥትሩ ቃል አቀባይ አኔ ኤክበርግ ገለጡ። ጠቅላይ ሚንሥትሩ አውሮፕላናቸው የስቶክሆልም አየር ማረፊያን እንደነካ በአምቡላንስ በፍጥነት ወደ ሐኪም ቤት መወሰዳቸው ተዘግቧል። አዲስ አበባ በተካሄደው የዓለም አቀፍ የልማት ጉባኤ ላይ ተሳታፊ የነበሩት የስዊድኑ ጠቅላይ ሚንሥትር ወደ ስዊድን ሲበሩ «ብርቱ ማቅለሽለሽ» እንደገጠማቸውም ተጠቅሷል። የጠቅላይ ሚንሥትሩ ቃል አቀባያዋ አኔ ኤክበርግ፣ ሚንስትሩ «የተወሰኑ ምርመራዎች ተደርጎላቸው ወደ ቤታቸው ይሄዳሉ» ሲሉ ለፈረንሣይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል። ስለጠቅላይ ሚንሥትሩ ኅመም ግን ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል። የ57 ዓመቱ የሶሻል ዴሞክራት ፖለቲከኛ ከዘጠኝ ወራት በፊት አንስቶ የስዊድን ጠቅላይ ሚንሥትር ናቸው።

Wednesday, 15 July 2015

አቶ አበበ ቸኮል ታሰረ

አቶ አበበ ቸኮል ታሰረ
የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ አበበ ቸኮል ታሰረ፡፡ አቶ አበበ አርብ ሀምሌ 3/2007 ዓ.ም የታሰረ ሲሆን ሀምሌ 4/2007 ዓ.ም ቄራ ፍርድ ቤት ቀርቦ ለሀምሌ 13/2007 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ ሰሞኑን የታሰሩት የመርከቡ ሀይሌና የደብሬ አሸናፊ ቤት መበርበሩም ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ሀምሌ 8/2007 ዓ.ም ለይግባኝ ጉዳይ ልደታ ፍርድ ቤት የቀረቡት እነ ወይንሸት ሞላ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን አላየሁትም በማለቱ ለሀምሌ 14/2007 ዓ.ም ተቀጥረዋል፡፡
በሌላ በኩል በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አቶ በፍቃዱ አበበ የመከላከያ ምስክሮቹ እየታሰሩበት እንደሆነ ገልጾአል፡፡ አቶ በፍቃዱ በመከላከያ ምስክርነት ሊያቀርበው የነበረው ወንድሙ ባንተወሰን አበበ እንደታሰረና ሌሎች የመከላከያ ምስክሮቹም በፖሊስ እየታደኑ እንደሆነ ገልጾአል፡

Saturday, 11 July 2015

የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ እስሩ ቀጥሏል

በአዲስ አበባና በየክፍለ ሀገሩ የሚገኙ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ እስሩ ቀጥሏል፡፡ ትናንትናው ዕለት በሸዋ ሮቢት የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪዎች የሆኑት አቶ ዘነበ ደሳለኝ፣ አቶ መንግስቱ ተበጀ፣ አቶ ቴዎድሮስ ሀብቴ እንዲሁም አዲስ አበባ ውስጥ አቶ ደብሬ አሸናፊ ታድነው የታሰሩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አቶ መርከቡ ሀይሌና አናኒያ ኢሳያስ ለእስር ተዳርገዋል፡፡
መርከቡ ሀይሌና አናኒያ ኢሳያስ ዛሬ ሀምሌ 4/2007 ዓ.ም ከጠዋቱ 4 ሰዓት ላይ አራት ኪሎ አካባቢ በፖሊስና ደህንነቶች ተይዘው ታስረዋል፡፡ እነ መርከቡ በተያዙበት ወቅት ፖሊስና ደህንነቶች ‹‹ብጥብጥ ልታስነሱ እየጣራችሁ መሆኑን ደርሰንበታል›› እንዳሉዋቸው ተገልጾአል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ስለሽ ደቻሳ ሀምሌ 1/2007 ዓ.ም ከቤቱ በደህንነትና በፖሊስ ታፍኖ ከፍተኛ ድብደባ ከተፈፀመበት በኋላ ታስሯል፡፡ ስለሽ ደቻሳ በተፈፀመበት ድብደባም እጅና እግሩ ላይ ስብራት እንደደረሰበት ታውቋል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ ታዛቢ የነበረው አስፋው ጀማል በትናንትናው ዕለት በፖሊስ ተይዞ መታሰሩን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ መርከቡ ኃይሌና አናኒያ ኢሳያስ በአራዳ ፖሊስ መምሪያ እንዲሁም ስለሽ ደቻሳ 6ኛ ፖሊስ ጣቢያ እንደታሰሩ ታውቋል፡፡
በተመሳሳይ እስሩ በየ ክፍለ ሀገሩን የቀጠለ ሲሆን በከፋ ዞን ጨላ ወረዳ 8 የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ‹‹ማዳበሪያ አልወስድም ብለዋል›› በሚል ለእስር እንደተዳረጉ ከቦታው የደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡ ሌሎች የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በማዳበሪያ ሰበብ ድብደባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የገለጹት የዞኑ የፓርቲው አስተባባሪዎች ነሲብ አደነ የተባለ የሰማያዊ ፓርቲ አባል ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበት ሆስፒታል ውስጥ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

የዞን 9 ጦማርያንን እና ጋዜጠኞችን አስመልክቶ የተሰጠ አጭር መግለጫ

የዞን 9 ጦማርያንን እና ጋዜጠኞችን አስመልክቶ የተሰጠ አጭር መግለጫ
የዞን ዘጠኝ ጦማርያን ሁለት አባላት እና ሶስት ጓደኞቻችንን መፈታት በመልካም ጎኑ የምንቀበለው ነው፤ ኢፍትሃዊ የሆነውን መታሰራቸውን፣ የስማቸውን መጥፋት ለአካላዊ እና ስነልቦናዊ ጉዳት መዳረጋቸው ፣ ከትምህርት እና ከሥራቸው መስተጓጎላቸው በቤተሰብ እና በወዳጆቻቸው ላይ የደረሰው እንግልት፣ በቸልታ የሚታለፍ ጉዳይ ባይሆንም ከ10 ተከሳሾች መካከል የአምስቱን ክስ መቋረጥ አዎንታዊ እርምጃ ጅምር ነውና ይበልጥ ሊበረታታ ይገባል፡፡ በተመሳሳይ ክስ የቀረበባቸው ቀሪ የዞን ዘጠኝ አባላት ማለትም ሶልያና ሽመልስ ( በሌለችበት) ፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አቤል ዋበላ እና አጥናፍ ብርሃኔ ከሌሎች ጓደኞቻቸው ተነጥለው እስካሁን መታሰራቸው እና ክሳቸውም አንደሚቀጥል መስማታችን ጉዳዬ አሁንም እጅግ በጣም አሳሳቢ እንደሆነ ያሳያል፡፡
የአምስቱ ክሳቸው የተቋረጠው ጓደኞቻችን ክስ በእርስ ከሚገኙት ጋር ተመሳሳይ በመሆኑ ቀሪ አራት ታሳሪ ጦማርያንን በእስር ለማቆየት የሚሰጥ ማንኛውም ምክንያት ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ እኛም በአምስቱ ወዳጆቻችን መፈታት ደስታችንን እየገለጽን አራቱ ቀሪ ጦማርያን እስኪፈቱ ድረስ የዞን9 ጦማርያን ይፈቱ የሚለው ጥያቄያቸን ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡
ይህ መልካም ጅምር አገራችን ጠባብ የፓለቲካ ምህዳር እና ዴሞክራሲያዊ መብቶች መታፈናቸውን እንዲቀይር ተጨማሪ የፓለቲካ እና የህሊና እስረኞችን በመፍታት አንዲጠናከር እየጠየቅን ከዚህ የአገሪቱን መልካም ስም ከሚያጠፉ ድርጊቶች መንግስት ራሱን ቆጥቦ ሁሉም ዜጋ የየራሱን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት በሩ ክፍት ይሆን ዘንድ አሁንም ማንኳኳታችንን ይቀጥላል፡፡ ለዞን9 ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኛ ቤተሰቦች ጓደኞች እና አጋርነታችን ስታሳዩን ለከረማችሁ ብዙዎች በዚህ አጋጣሚ ከፍተኛ ምስጋናችንን እናቀርባለን ፡፡
የሽብር ክስ የቀረበባቸው እና የተፈቱትም ሆነ አሁንም ክሳቸው ይቀጥላል ተብሎ በእስር የሚገኙ ጓደኞቻችን ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ ሕገ መንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀማቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉ መሆናቸው ይታወሳል፡፡
አሁንም ስለሚያገባን እንጦምራለን፡፡
ዞን9

በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ተከፈተው የእስር ዘመቻ ዛሬም ቀጥሏል


በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ተከፈተው የእስር ዘመቻ ዛሬም ቀጥሏል
ዛሬ ሐምሌ 4 2007ዓ.ም ረፋዱ ላይ አቶ መርከቡ ሃይሌ ሰሞኑን ሲከታተሉት በነበሩ ደህንነቶች እና ፖሊስ ታፍኖ ለጊዜው ወደአልታወቀ ቦታ ተወስዷል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ ትናንት በኢህአዴግ የታሰረው አቶ ደብሬ አሸናፊ ዛሬ ረፋዱ ላይ ቤቱ በከፍተኛ የታጠቁ ሃይሎች ተከቦ ፍተሻ የተካሄደበት ሲሆን አሁን በጉለሌ አካባባቢ ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ እንደሚገኝ ተረጋጧል፡፡
በሌላ በኩል ትናንት ታፍነው የታሰሩት በሰሜን ሸዋ የሰማያዊ ፓርቲ የተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ የነበሩትን አቶ ዘነበ ደሳለኝ፣ የፓርቲው ንብረት ያዥ የሆኑትን አቶ መንግስቱ ተበጀና የቀድሞው አንድነት የቀጠና አመራርና በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ የሆኑትን አቶ ቴዎድሮስ ሀብቴ ውጬ አቶ ምንተስኖት ወንዳፈራሁ እና አቶ ብሩ አይደፈር የተባሉ የሰማያዊ አባላት ታፍነው መታሰራቸውን ታውቋል፡፡

Thursday, 9 July 2015

የጣይቱ ልጅ!!

የርዕዮትን: የማህሌትንና የኤዶምን ከህወሀት ማጎሪያ እስር ቤት ነጻ መሆን ውስጤ የፈጠረውን �ደስታ እያጣጣምኩ እያለ ድንገት በትዝታ አምስት ወራት ወደ ሁዋላ ሄድኩኝ- -ከኤርትራ በረሃ:: ይህቺን ኢትዮጵያን ከህወሀት እስር ቤት ነጻ ለማውጣት ብረት ያነሳችውን እህታችንን ላስተዋውቃችሁ::
አርበኛ ሀና ትባላለች:: የ23 ዓመት ወጣት ናት:: የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋጊ ወታደር ስትሆን በተለያዩ አውደ ውጊያዎች ተሳትፋለች:: በኤርትራ በረሃ ስማቸው ከጀግንነት ጋር ከሚነሳላቸው አርበኞች መሃል ሀና ግንባር ቀደም ናት:: ስሟ በአርበኞች መንደር ገኖ ይነሳል::
.........አንድ ጊዜ ላይ እንዲህ ሆነ:: 
ሀና የምትገኝበት ወታደራዊ ክፍል ግዳጅ ይሰጠዋል:: እስከ 30 የሚጠጋ አርበኛ የሚገኝበት ይህ ቡድን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጦ በመግባት በአንድ የህወሀት ወታደራዊ ካምፕ ላይ ጥቃት ፈጽሞ የመመለስ ግዳጅ ተሰጥቶት ይሰማራል:: ሀና መትረየሷን ታጥቃለች:: ጠዋት ከመነሻቸው ወደ ኢላማ ቦታው ገሰገሱ:: እንደታቀደው ድንገተ�ኛ ጥቃቱ ተሰንዝሮ የታሰበውን ጉዳት አድርሰው ወደ ካምፓቸው ሊመለሱ እያለ ድንገት በህወሀት ሰራዊት ይከበባሉ:: ምን ይደረግ? ብዙ ቁጥር ያለውንና እስከአፍንጫው የታጠቀውን የህወሀት ሰራዊት መክቶ ወደ ካምፕ መመለስ ከባድ ሆነ:: የዚህን ጊዜ ነበር አንድ ጀግና ታሪክ የሰራችው:: ....ሀና::
መትረየሷን መተረች:: ገዢ መሬት ያዘች:: ቦታዋን አስተካከለች:: ....እሷ መስዋዕት ሆና የትግል ጓዶቿን ልታስመልጥ ወሰነች:: ምሽት እየመጣ ነው:: ጓዶቿ ተ�ስናበቷት:: ዳግም በህይወት እንደማያገ�ኟት ታወቃቸው:: ...እሷ መትረየሷን ወደ ህወሀት ሰራዊት ለቀቀችው:: ለጓዶቿ ሽፋን በሚሰጥ ስልት አስካካችው:: ...ፍልሚያው በአንዲት ሀና እና በህወሀት ሰራዊት መሃል ሆነ:: የሀና መትረየስ ያስካካል:: ጓዶች በዚያ ሽፋን ወደ ጦር ካምፓቸው እየተመለሱ ነው:: የሀና የመትረየስ ድምጽ እየራቃቸው ነው:: እነሱ ይተርፉ ዘንድ አንድ አርበኛ መስዋዕት መሆን ግድ አለ:: በተሰጣቸው ግዳጅ ውጤታማነት እየተደሰቱ የሃናን መስዋዕትነት እያወደሱ ከካምፓቸው ምሽት ላይ ደረሱ:: በአርበ�ኞች መንደር ህይወት እንዲህ ናት:: ታጋይ ይሰዋል:: ትግል ይቀጥላል::
...እኩለ ሌሊት ከመድረሱ በፊት ነው:: ጭው ካለው የኤርትራ በረሃ አንድ ሰው ወደ አርበኞቹ መንደር ከኢትዮጵያ ድንበር አቅጣጫ ይገሰግሳል:: በርቀት የተመለከቱት የሌሊት የካምፕ ተረኛ ዋርዲያዎች(ጠባቂዎች) መሳሪያቸውን አስተካክለው ጣት ከቃታ አገናኝተው ወደ ካምፑ እየገሰገሰ ያለውን ሰው ይጠብቃሉ:: ውድቅት ሌሊት ስለነበር ማንነት መለየት አልተቻለም:: የሚገሰግሰው ሰው እየቀረበ ሲመጣ ዋርዲያዎቹም ኢላማቸውን አስተካክለው እርምጃ ለመውሰድ ተ�ዘጋጁ:: ....ሰውዬው ቀረበ:: ሴት ናት::ሃና:: ዋርዲያዎቹ አላመኑም:: የዕለቱን የይለፍ ቃል ጠየቋት:: መለሰችላቸው:: ደክሟታል:: ተአምር የሚያሰ�ኘው ከዚይ የህወሀት ሰራዊት ከበባ ማምለጧ አይደለም:: ሁለት የጦር መሳሪያዎችንም ማርካ ተሸክማለች:: ከሷ መትረየስ ጋር ሶስት:: ዋርዲያዎቹ በሚያዩት ነገር ተደንቀዋል:: በአርበኞች መንደር ስለ ሃና እርም ወጥቷል:: ጉድ ተባለ::
....ሃናን በአካል ሳገኛት በጣም ቁጥብ ነበረች:: ብዙ አትናገርም:: ታሪኳን እንድታጫውተኝ ያደረኩት ጥረት አልተሳካም:: ሲበ�ዛ ዝምተኛ ናት:: ጀግና አይናገርም::
...ሃና ከሰሞኑ ውጊያዎች በአንዱ እንደተሰለፈች እገምታለሁ:: ልብን በኩራት በሚያሞቀው ጀግንነቷ ሁሌም አስታውሳታለሁ:: የጣይቱ ልጅ!!!!!


Tuesday, 7 July 2015

አርበኞች ግንቦት 7 በተለያዩ ግንባሮች በወያኔ ላይ የከፈተውን ማጥቃት ተከትሎ ከወያኔ ጎራ የተምታቱ ዜናዎች እየተደመጡ ነው።

አርበኞች ግንቦት 7 በተለያዩ ግንባሮች በወያኔ ላይ የከፈተውን ማጥቃት ተከትሎ ከወያኔ ጎራ የተምታቱ ዜናዎች እየተደመጡ ነው።
ቀደም ሲል የተሰነዘረባቸውን ጥቃት “ምንም ነገር የለም” ብለው ለማድበስበስ የሞከሩት የወያኔ ሹማምንትና ካድሬዎች ዜናው በኢሳት ቴሌቪዥን፣ ሬድዮ፣ በተለያዩ ድረ-ገጾች እና በዋንኛነት ደግሞ በማህበራዊ መገናኛ ገጾች በስፋት በመዘገቡ “ምንም ነገር የለም” ከሚለው ወደ ተምታታ ዜና ማሰራጨት ተሸጋግረዋል።
የወያኔዎቹ ቃል-አቀባይ ጌታቸው ረዳ በሚሚ ስብሃቱ ኤፍ ኤም ራድዮ ላይ ቀርቦ “በአካባቢው በመሬት የተነሳ መጠነኛ ግጭት ነበር” በማለት ሁኔታውን ከገለጸ በኋላ ወድያውም “በሻብያ ላይ የማያዳግም ቅጣት” ሊሰነዝሩ እንደሚችሉ ተናግሯል።
አይጋ ፎረም የሚባለውና በአፍቃሪ ወያኔነቱ የሚታወቀው ድረገጽ ደግሞ የመከላከያ ሰራዊቱ በሻብያ ...ተላኩ ያላቸውን ታጣቂዎች መማረኩን ዘግቧል።
አነጋጋሪ የሆነውና ምናልባትም አብዛኞችን ፈገግ ያደረገው ዜና ደግሞ ኣሻንጉሊቱ ኃይለማርያም ደሳለኝ ለአሻንጉሊቱ የተወካዮች ምክር ቤት ያደረጉት ንግግር ነው፣ “ህዝብን አስፈቅደን ከሻብያ ጋር ጦርነት እንገጥማለን” ነበር ያሉት ኃይለማርያም ደሳለኝ።
የወያኔ ሹማምንት ጥቃት እየሰነዘረባቸው ያለውን “አርበኞች ግንቦት 7ን” በስም ለመጥቀስ እጅግ የፈሩ ይመስላሉ።
አርበኞች ግንቦት 7ን በስም መጥቀስ ለምን ፈሩ? ብሎ ለሚጠይቅ መልሱ ቀላል ነው።
ህዝብ የአርበኞች ግንቦት 7 የነጻነት ታጋዮች ከአብራኩ የወጡ የቁርጥ ቀን ልጆቹ እንደሆኑ ያውቃል። ስለዚህም ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ጦርነት ልንገጥም ነው ቢሉ ማንም እንደማይተባበራቸው ይረዳሉ። ያላቸው እድል “ሻብያ” እያሉ መለፈፍ ነው።
የኢትዮጵያ ህዝብ የጦርነትን አስከፊ ገጽታ ይገነዘባል ይሁንና የወያኔ አስከፊ ዘረኛ ስርዓት እያደረሰበት ካለው የመረረ ጭቆና ጋር በማነጻጸር ይመስላል አርበኞች ግንቦት 7 በወያኔ ላይ የሰነዘረውን ጥቃት በደስታ ነው የተቀበለው።
በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ኢሳት ቴሌቭዥን በመደወል ደስታቸውን ሲገልጹና ለአርበኞቹም መልካሙን ሁሉ ሲመኙ ተደምጠዋል።

Sunday, 5 July 2015

, Serkalem Selassie and her 9-year-old son, Nafkot, protested President Obama’s upcoming trip to Ethi­o­pia

D.C.-area Ethiopians say Obama trip will send wrong signal to repressive regime in homeland
Near the White House on Friday, Serkalem Selassie and her 9-year-old son, Nafkot, protested President Obama’s upcoming trip to Ethi­o­pia. As a journalist in her homeland, she was jailed, and Nafkot was born while she was in prison. She has political asylum now. (Evelyn Hockstein/For The Washington Post)
By Pamela Constable July 3
...
When Barack Obama entered the White House, many Ethio­pian immigrants in the Washington area cheered. When he gave a speech in Ghana in 2009, vowing to promote democracy and human rights across Africa, they were thrilled. But now that Obama will soon visit Ethi­o­pia, many members of the region’s largest African emigre group are up in arms.
Their concern is that his trip later this month — the first by a sitting American president — will send the wrong message and bolster a regime that has intimidated opponents, manipulated elections and sent dozens of journalists to prison.
“Mr. Obama is supporting a dictatorship and giving legitimacy to tyranny,” declared Serkalem Selassie, 39, a refu­gee in Arlington. “Day by day, things are getting worse. There is no freedom to speak, to meet. Anyone who writes can be jailed for associating with terrorism.”
For Selassie, a former newspaper publisher who fled her homeland two years ago and now works at a parking garage, the anger is deeply personal.
Her husband, journalist Eskinder Nega, is in prison serving an 18-year sentence for treason. Selassie was also sent to jail in 2005, and her son Nafkot, 9, was born while she was in custody. She has not been permitted to communicate with her husband in two years.
“No photos, no letters — nothing is allowed,” said Selassie, stylish but haggard-looking. Her son still suffers from his experiences as a young child. “He saw them take his father away in handcuffs and call him a terrorist,” she said. “He kept asking what that meant.”
Obama’s trip will underscore the delicate balancing act of U.S. relations with the Addis Ababa government, a crucial ally in a volatile region that also regularly flouts democratic norms. The ruling party has maintained power for 24 years since the violent overthrow of a Marxist dictator.
U.S. officials have long praised the government in Addis Ababa for its success in economic development and food security, its reliability as an ally in the war on terror and its generous supplying of troops for U.N. peacekeeping missions. In turn, the United States sends substantial amounts of aid.