Wednesday, 15 July 2015

አቶ አበበ ቸኮል ታሰረ

አቶ አበበ ቸኮል ታሰረ
የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ አበበ ቸኮል ታሰረ፡፡ አቶ አበበ አርብ ሀምሌ 3/2007 ዓ.ም የታሰረ ሲሆን ሀምሌ 4/2007 ዓ.ም ቄራ ፍርድ ቤት ቀርቦ ለሀምሌ 13/2007 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ ሰሞኑን የታሰሩት የመርከቡ ሀይሌና የደብሬ አሸናፊ ቤት መበርበሩም ታውቋል፡፡ በተመሳሳይ ዛሬ ሀምሌ 8/2007 ዓ.ም ለይግባኝ ጉዳይ ልደታ ፍርድ ቤት የቀረቡት እነ ወይንሸት ሞላ ፍርድ ቤቱ መዝገቡን አላየሁትም በማለቱ ለሀምሌ 14/2007 ዓ.ም ተቀጥረዋል፡፡
በሌላ በኩል በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኘው የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አቶ በፍቃዱ አበበ የመከላከያ ምስክሮቹ እየታሰሩበት እንደሆነ ገልጾአል፡፡ አቶ በፍቃዱ በመከላከያ ምስክርነት ሊያቀርበው የነበረው ወንድሙ ባንተወሰን አበበ እንደታሰረና ሌሎች የመከላከያ ምስክሮቹም በፖሊስ እየታደኑ እንደሆነ ገልጾአል፡

No comments:

Post a Comment