Thursday, 30 April 2015

ኢትዮጵያ እሥር ላይ የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙን፤ ቪየትናም ደግሞ የኢንተርኔት ፀሐፊዋን ወይም ብሎገሯን ታ ፎንግ ታንን እንዲለቅቁ ዩናይትድ ስቴትስ ጠየቀች፡፡

ኢትዮጵያ እሥር ላይ የምትገኘውን ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙን፤ ቪየትናም ደግሞ የኢንተርኔት ፀሐፊዋን ወይም ብሎገሯን ታ ፎንግ ታንን እንዲለቅቁ ዩናይትድ ስቴትስ ጠየቀች፡፡


የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቃል አቀባይ ጄፍ ራትካ ናቸው ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ይህንን የመንግሥታቸውን ማሳሰቢያ ያስተላለፉት፡፡የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በዚህ ሣምንት እያወጣቸው ባሉ ተከታታይ የፕሬስ መግለጫዎች በዓለም ዙሪያ በየእሥር ቤቱ ያሉ ጋዜጠኞችን በየቀኑ እያነሣ ይገኛል፡፡
በዚህ “FREE THE PRESS” ወይም “ፕሬስን ነፃ አውጡ” በሚለው ዘመቻው የዛሬው የመሥሪያ ቤቱ መግለጫ ካተኮረባቸው ሁለት ጋዜጠኞች አንዷና ቀዳሚዋ የቀድሞ የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የእንግሊዝኛ መምህር ኢትዮጵያዊቱ ፍሪላንስ ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ነች፡፡በፀረ-ሽብር ሕጉ መሠረት በተመሠረተባት ክሥ ጥር 10/2004 ዓ.ም ተፈርዶባት እስከዛሬ ወኅኒ ቤት እንደምትገኝ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ቃል አቀባይ ጄፍ ራትካ ጠቁመዋል፡፡
ርዕዮት ኢትዮጵያ ውስጥ ከሥራቸው ጋር በተያያዘ በተመሠረቱባቸው ክሦች ምክንያት ከታሠሩ 18 ጋዜጠኞች አንዷ ስትሆን ይህ ሁኔታም ኢትዮጵያ በአህጉሩ ብዙ ጋዜጠኞችን በማሠር ቀዳሚዋ እንድትሆን አድርጓታል ብለዋል፡፡
ርዕዮት የመንግሥቱን ፖሊሲዎች የሚተቹ ፅሁፎችን በጋዜጣ በማውጣቷ ምክንያት በሰኔ 2003 ዓ.ም ተይዛ የሽብር ፈጠራ ክሥ ከተመሠረተባት በኋላ የ14 ዓመት እሥራት ተፈርዶባት እንደነበረ ያስታወሱት ራትካ የእሥራት ዘመኗ ወደ አምስት ዓመት ዝቅ እንዲል ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ በነሐሴ 2004 ዓ.ም መወሰኑን ተናግረዋል፡፡
ይሁን እንጂ ክሡ ሙሉ በሙሉ እንዲሠረዝላት በተከታታይ ያቀረበቻቸው የይግባኝ አቤቱታዎች ውድቅ መደረጋቸውንም ራትኮ አመልክተዋል፡፡
ሃሣብን የመግለፅ ነፃነት መብቷን ተግባራዊ በማድረጓ ብቻ ታሥራ የምትገኘውን ርዕዮትን እንዲፈታ ለመንግሥቱ ጥሪያችንን እናቀርባለን – ያሉት ራትኮ – መንግሥቱ ፀረ-ሽብር አዋጁን ሃሣብን በነፃነት የመለዋወጥን ተግባር ለመጠምዘዝ ጉዳይ ከመጠቀም እንዲቆጠብም እናሳስባለን …” ብለዋል፡፡
የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ቃል አቀባይ ጄፍ ራትኮ በመቀጠልም በአውሮፓ የዘመን አቆጣጠር የ2013 ዓ.ም ጀብዱ ፈፃሚ ሴቶች ዓለምአቀፍ ሽልማት ያሸነፈችውና የቪየትናምን መንግሥትና ኮምዩኒስት ፓርቲውን የሚተቹ ፅሁፎችን ኢንተርኔት ላይ በማውጣቷ የአሥር ዓመት እሥራት ተፈርዶባት ወኅኒ የምትገኘው ታ ፎንግ ታንን የቪየትናም መንግሥት በአፋጣኝ እንዲለቅቅ መንግሥታቸው እንደሚያሳስብ አስታውቀዋል፡፡

Wednesday, 29 April 2015

ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች እየለጠፉ መሆናቸው ተገለፀ

ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች እየለጠፉ መሆናቸው ተገለፀ
የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሰማያዊን ፖስተሮች ባልተፈቀዱ ቦታዎች በመለጠፍ ላይ መሆናቸውን ሰማያዊ ፓርቲ ለምርጫ ቦርድ በፃፈው ደብዳቤ አሳወቀ፡፡ ፓርቲው ለምርጫ ቦርድ በፃፈው ደብዳቤ አዲስ አበባ ውስጥ በትምህርት ቤቶች፣ በቤተ ክርስቲያናት፣ በወታደራዊ ካምፖች እንዲሁም በሌሎች ፓርቲዎች ዕጩ ፖስተሮች ላይ ያለ ፓርቲው ዕውቅና የሰማያዊ ፓርቲ ፖስተር እየተለጠፈ እንደሚገኝና ይህም የገዥው ፓርቲ ካድሬዎች የሚፈጽሙት ተግባር እንደሆነ ገልጾአል፡፡
ይህንንም ተከትሎ ምርጫ ቦርድ ‹‹ሰማያዊ ፓርቲ በተከለከሉ ቦታዎች ፖስተር እየተለጠፈ ነው›› የሚል ቅሬት በማቅረቡ ምን አልባት አባላት ተሳስተው ለጥፈው ይሆናል ብለው ፖስተሮቹን እንዳነሱ የገለጸው የፓርቲው የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ ወጣት እያስፔድ ተስፋዬ ፖስተሮቹን ካስነሱ በኋላ በድጋሜ እነዚህ ቦታዎች ላይ ያለ ሰማያዊ እውቅና ፖስተሮቹ ተለጥፈዋል ብሏል፡፡ ፖስተሮቹን ለሁለተኛ ጊዜ ለማንሳት የሄዱት የሰማያዊ ፓርቲ አባላትም መታሰራቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡
ወጣት እያስፔድ አክሎም ‹‹ከሰማያዊ ፓርቲ እውቅና ውጭ ፖስተሮች እየተለጠፉ ያሉት ገና ሰማያዊ ፖስተር ባልለጠፈባቸው አካባቢዎች ነው፡፡ እኛ ስናነሳ ደግመው ይለጥፋሉ፡፡ ለማንሳት የሚሄዱ አባላትንም ያስራሉ፡፡ ይህን እኩይ ድርጊትም ገዥው ፓርቲ ነው የሚፍጽመው ብለን እናምናለን፡፡ ይህን እያደረገ ያለው ሰማያዊን ሆን ብሎ ለመክሰስ ነው፡፡ ይህንንም ለምርጫ ቦርድ አሳውቀናል፡፡›› ሲል ገልጾአል፡፡ ፓርቲውም ‹‹ይህን ድርጊት ፓርቲያችን እንደፈፀመው ተደርጎ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት በኩል የተሰጠው ማሳሰቢያ ፓርቲያችን አይመለከተውም›› ሲል በደብዳቤው አሳውቋል፡፡

የወያኔ ቡድንን እስከመጨረሻው እናስወግደው

የወያኔ ቡድን ለህዝብ ደንታ እንደሌለው በተለያዩ አጋጣሚዎች እያሳየ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ህዝብ ስደትን በይፋ የጀመረው ህዝባዊ መንግስት ይቋቋም፤ የሴቶች መብት ይከበር፤ ዲሞክራሲ ያለገደብ፤ እና የተለያዩ የእኩልነት እና የነጻነት ጥያቄ በማንሳታቸው በፖለቲካ አስተሳሰባቸው እና ያለውን መንግስት በመቃወማቸው የደርግ ስርአት ያደርግ የበነበረውን አሰቃቂ ግርፋት ግድያ በአጠቃላይ ስርዓቱ የፈጠረውን አፈናና እና ግፍ ሽሽት እንደሆነ ይታወቃል። ዛሬ ደግሞ በአይነቱም ሆና በብዛቱ ተባብሶ ይገኛል። ህዝባችን ሃገሩ ያለውን ችግር ቢሸሽም ሸሽቶ የሚሄድባቸው ሃገራት ያለውን ሃገር አጥፊ ስርዓት ደጋፊ በመሆናቸው እንደዚሁም የተለያዩ ሃገራት መፈራረስ እና የተለያዩ አሸባሪ ቡድኖች በየቦታው መፈልፈል ከሃገራቸው በስርዓቱ በደል የተሰደደው የኢትዮጵያ ህዝብ በሚሄደበት መንገድም ሆነ በደረሰበት ሃገር ሁሉ እየተገፋ እና እየተሰቃየ መራራ እና አስከፊ ጊዜ እያሳለፈ ይገኛል።
ህዝባችን በተለያዩ ሃገራት ለምሳሌ በየመን የተለያየ ግፍ እና መከራ ሲያሳልፍ መቆየቱ የሚታወስ ነው።በአሁኑ ሰአት ደግሞ የisis ወደ የመን መግባት አስጨንቆት የይድረሱልን ጥሪ እያሰማ ይገኛል።በደቡብ አፍሪካ ያለውም ሁኔታ ሙሉ በሙሉ እንዳልተረጋጋ እዛው ያሉ ወገኖች ይናገራሉ። በሊቢያም ሌሎች ዜጎቻችን በቅርቡ ያሳለፉትን አሰቃቂ ድርጊት እንዳይደግሙ የብዙዎቻችን ስጋት ነው። በአረብ ሃገራትም የሚኖሩ እህቶቻችን እየደረሰባቸው ያለውን መቋቋም እያቃታቸው እንደሆነ የሚያሳዩ ምልክቶች እየጨመሩ ናቸው።በአውሮፓም ቢሆን የሚደርስብን እንግልት ቀላል የሚባል አይደለም።ባለውለታቸው ነን ብንቸገር ይደርሱልናል ብለን የምናስባቸው ሃገራት ጭራሽ የችግራችን አባባሽ ሆነው ተገኝተዋል ሲሰደዱ የተቀበልናቸው በችግራቸው የደረስንላቸው ውለታችን ከምንም እንደማይቆጥሩት በተግባር አሳይተውናል።
እዚህ ላይ የሚገርመው ከየአቅጣጫው ህዝባችን ለሚደርስበት ችግር የድረሱልኝ ጥሪ የሚያሰማው በተቃዋሚ ሚዲያዎች እንደነ ኢሳት እና ፍኖተ ሬድዮ ላይ መሆኑ ነው። ይህ የሚያሳየው ህዝባችን ባለው ስርአት ምን ያህል ተስፋ እንደቆረጠ ነው።ህዝባችን መንግስት አልባ ነው የሚለውንም ማረጋገጫ ነው።
በመንግስት ስም የተቀመጠው የወያኔ ቡድን ለህዝብ ደንታ እንደሌለው በተለያዩ አጋጣሚዎች እያሳየ ይገኛል። እንኳንስ ለወገን ሊቆረቆር በሃገር ውስጥ በውጭ ሃገራት የሚደርስብንን በደል ለመቃወም የሚወጡትን የወገን ተቆርቋሪዎች በመደብደብ እና በማሰር ከህዝብ ጎን ከመሰለፍ ይልቅ ህዝብን ከሚያንገላቱት ጎን መቆሙን አሳይቶናል።በሳኡዲ የተቃወሙት ላይ ያደረሰውን ድብደባ ሳንረሳ በሊቢያ isisን ለመቃወም በወጡት ላይ ደግሞታል ይባስ ብሎ ለህዝብ መቆርቆር እና ለወገን ማልቀስን እንደአሸባሪነት ቆጥሮ እየደነፋ ይገኛል።የተለያዩ ሃገራት ከየመን ዜጎቻቸውን በቻሉት ሁሉ እያወጡ ወገንተኛነታቸውን እያሳዩ ባለበት ሰአት ወያኔ የመረጠው በቃላቀባዩ የፌስቡክ ለበጣን ሆኖ ተገኝቷል።ዳሩከዝንብ መቼስ ማር ይጠበቅ እና
ታዲያ የሚያሳዝነው ህዝባችን ይህን ሁሉ መስዋእትነት የሚከፍለው በአምባገነኖች በጠባቦች በባንዳዎች በሆድ አደሮች በንዋይ ናፋቂዎች እና በባእዳኖች መሆኑ ነው። እንደነዚህ አይነት ጥርቅሞች ደግሞ ለወገን ይቆረቆራል ወይም ለሃገር ያስባል ማለት ቀሚሰ ተስፋ ነው።ባእዳኖቹም ቢሆኑ የራሳቸውን ጥቅምትተው ለሃገራችን ያስባሉ ብሎ መጠበቅ ሞኝነት ነው።
እንደማንኛውም የህብረተሰብ ጥርቅም እንደነዚህ አይነቶች በሃገራችን ቢኖሩም እራሳቸውን ለሃገራቸው ያሳለፉ እድሜያቸውንም በትግልእየጨረሱ ያሉ እንዳሉ ማወቁ ተገቢ ነው። በአሁኑ ሰአት እንደሚታየውም ከሆዳሞቹ ከባንዳዎቹ ከጠባቦቹ ቁጥር ይልቅ የሃገር ተቆርቋሪው የአንድነት ሃይሉ ሚዛን እየደፋ መጥቷል። ወያኔም እርቃኑን መቅረቱም በቅርቡ ያየነው እውነታ ነው። በመሆኑም የተጀመረው የህዝብ ትግል ከዳር ይደርስ ዘንድ በየቦታውየሚሰቃየው የህዝባችን ሰቆቃ ይቆም ዘንድ የራሳችን የሆነ የሚቆረቆርልን በህዝብ የተመረጠ መንግስት ይኖረን ዘንድ ከእስከዛሬው በበለጠ ተደራጅተን እና አንድ ሆነን ትግላችንን በማጠናከር ይህን ኢትዮጵያን ለማጥፋት የተነሳው የወያኔ ቡድንን እስከመጨረሻው እናስወግደው።
ህዝብ ያሸንፋል!!!!!!!!!!!!

የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ

የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ
የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።

ሰው በአሹቅ ብቻ አይኖርም !


ሰው በአሹቅ ብቻ አይኖርም !
(አሌክስ አብርሃም)
‹‹ጥጋብ ፍንቅል አድርጓችሁ ነው የተሰደዳችሁት እንጅ …አገራችሁ ማሩ ወተቱ …›› ማለት ‹‹ጠግባችሁ ሂዳችሁ ነው የታረዳችሁት እንኳን የእጃችሁን አገኛችሁ ›› ከማለት አይተናነስም !!አሁን ከትላንት ወዲያ ታዋቂው የማስታወቂያ ባለሙያ አርቲስት ሰዊት ፍቅሬ ጨርቆስ ሃዘን ቤቱ ንግግር እንዲያደርግ ተፈቅዶለት በሚያስገመግም ድምፁ እንዲህ አለ ‹‹ ከሰው አገር ወርቅና ብር እናታችን እቅፍ ውስጥ አሹቅ እየበላን ሙቆን ብንኖር ይሻላል›› ቆይ እውነቱን እናውራ እንጅ ! የታለ ጥጋቡ … የታለ ስራው … የታለ አሹቁ….እንዴዴ ….ምናይነት በሰው ህይዎት ላይ መቀለድ ነው ይሄ ! ሰው እኮ እንስሳ አይደለም …በልቶ ጠጥቶ ሆዱ ከሞላ መተኛት ብቻውን በቂ ነው ሊባል አይገባም !
እከሌ መቶ ሽ ብር ከፍሎ ተሰደደ ለምን እዚሁ አይሰራባትም የሚል የዋህ ሒሳብ የሚያሰሉ ሰዎች ገጥመውኛል ….እጁ ላይ አፈር ከድቤ በልቶ ያጠራቀማትን ገንዘብ እየበላ አጨብጭቦ ከሚቀር ....ስደት ላይ ኢንቨስት ሊያደርግ ወሰነ በቃ ….ለምን አገሩ ላይ ስራ አይሰራባትም ….አገራችን ላይ ስራ እድል በሆነበት በዚህ ጊዜ መቶ ሽ ብር ምን እንደሚሰራ ሁላችንም እናውቃለን ….ቤት ልከራይ ቢባል የስድስት ወር ኪራይ የአመት ኪራይ በአንዴ በሚጠየቅባት አገር ….መቶ ሽ ብር እና ከዛ ያነሰ ብርን እንደትልቅ ካፒታል የሚቆጥር ሰው …ምናልባት ነፍሱ ድሮ ላይ የቆመ ሰው ይሆናል !
እናቴ ያሳደገችኝ እኮ እሷ ስር ተወሽቄ አሹቅ እንድበላ አይደለም ! የተሻለ ኑሮ እሻለሁ …ለእናቴ ላሳልፍላት እፈልጋለሁ … ቤት እፈልጋለሁ የተሻለ ትምህርት እፈልጋለሁ ማግባት መውለድ ለቤተሰቤ አለኝታ መሆን እፈልጋለሁ ! ልጆቸ ጥሩ ትምህርት ቤት እንዲማሩ ጥሩ እውቀት እንዲኖራቸው እፈልጋለሁ ….አሹቅ እየበላሁ ነገ ይሄንኑም አሹቅ ያጡ ልጆችን መፍጠር አልሻም ! አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ህዝብ የሚሰደደው ደላላ ስለደለለው ወይም አገሩን ስለጠላና …አገሩ ላይ ((ሚሊየነር መሆን ስለደበረው)) አይደለም ! ከእለት ጉርስ ያለፈ ነገር ማግኘት ዘበት ስለሆነበት ለፍቶ ጠብ የሚል ነገር ስላጣ ነው !! ዛሬን ብቻ አይደለም ማሰብ …ዛሬ ለፍቶ ጉልበቱን ገብሮ ይኑር ነገስ እድሜው ሲገፋ ነገስ ልጆች ሲወልድ ….ነገስ ነው ጥያቄው ! እህት ወንድሞቹ ለእግራቸው ጫማ ሲያጡ እየተመለከተ አሹቁን እየቃመ ቁጭ የሚል ልብ ያለው ሰው የለም !
ተው እንጅ ባለቢላዎቹ ሲገርሙን የብሶት አንገታችንን በቃል ስለታችሁ አትረዱን ! በመጀመሪያ ድግሪ ሁለት ሽ ብር እንኳን በማትከፍል አገር … ጠግባችሁ ተሰደዳችሁ ይባላል እንዴ ….ስደት በባህሪው እኮ ተፈጥሯዊ ህግ አለው ….ካልተሸለ ቦታ ወደተሸለ ቦታ መሄድ ማለት ነው ! አገራችን የተሻለች ብትሆንማ እንኳን እኛ ልንሄድ ሌሎችም ወደኛ በተሰደዱ ነበር ! ጠላታችን ድህነት ነው ብለን አውጀናል እኮ … አቅም ያለው ድህነትን ይፋለመው አቅም ያጣ ደግሞ ከጥላት ቀጠና ማፈግፈጉ የጦርነት ህግም ነው ! ጦርነት እውነት ነው ጨካኝ ጠላት ነው ….በመፎክር ብቻ አይመለስም ! ስጋህን ብቻ ሳይሆን ነፍስህንም አጋድሞ ያርድሃል !
ድህነት ያባረረውን ህዝብ ስደተኛን ተቀባዮቹ ግፍ ዋሉበት ይሄ ነው እውነቱ ! እስቲ አሁን ዝቅ ብሎ መስራትን ከጨርቆስ ልጆች የበለጠ ማን ያውቃታል …. ዝቅ ተብሎም ጠብ የሚል ነገር ጠፋ ሄዱ ! እና ስራ ንቀው እንል ዘንድ ተገቢ ነው እንዴ …. ለምን ወሬ እናሳምራለን …. አስር ጊዜ ‹‹ደላላ እያታለላቸው ›› ይላል ሚዲያው …ከኑሯችን የበለጠ ደላላ የለም ! እንደውም ለስደት የሚገፋፉ አንደኛ ደላሎች የማስታወቂያ ባለሙያዎች ናቸው !
አሹቅ ብሉ ዳቦ ብሉ ….የተፈጠርኩት አሹቅ እየበላሁ ጮማ የሚቆርጡ ሰዎችን ምራቄን እየዋጥኩ እንድመለከት አይደለም ! ለዚህ ደግሞ ሰው ነኝና መጀመሪያ አገሬ ላይ አቅሜ የፈቀደውን ሁሉ ለመስራት እሞክራለሁ …. አገሬ የልፋቴን ካልከፈለችኝ በተለይ ደግሞ ከእኔ በታች የሚደክሙትን እያነሳች አናቴ ላይ ካስቀመጠች … ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ከሌለ …ከሰውነቴ ይልቅ ባለኝ ገንዘብና ደረጃ የምመዘን ከሆነ ….እንደሰው የምቆጠርበት ተንቄም ቢሆን የተሸለ የገንዘብ አቅም የተሸለ ነገር የማገኝበት ቦታ ሁሉ ምርጫየ የማይሆንበት ምክንያት የለም !
‹‹እናትህ እቅፍ ውስጥ ሁነህ አሹቅም በልተህ ቢሆን መኖር ይሻላል ››ይሉት ቀልድ …አሹቅ እየበላህ የእኔን ማስታወቂያ እየተመለከትክ በአምሮት ኑር ከማለት ውጭ ምን ትርጉም ይኖረዋል ! እንዴ ራሳቸው የማስታወቂያ ባለሙያዎቹ አይደሉ እንዴ …‹‹ለበዓል ለእናትሽ ብር ላኪ በዚህ ባንክ መንዝሪ›› እያሉ የተሰደደው ሁሉ ሃብታም የተሰደደው ሁሉ ላኪ መንዛሪ መሆኑን እንቁልልጭ እያሉ ለስደት የሚገፉን …የምን ዞሮ ‹‹አሹቅ ቂጣ›› እያሉ በሰው ቁስል እንጨት መስደድ ነው ! እስቲ ሃቁን እናውራ በቴሌቪዥን ከሚሰራጩ ማስታወቂያዎች አንድ እንኳን ‹‹የአሹቅ በሊታዎች›› ማስታወቂያ አይታችሁ ታውቃላችሁ ?…. አሹቅ እየበላሁ ነው ኢንሹራንስ የምገባው? ….አሹቅ እየበላሁ ነው የተንፈላሰሰ ቪላ በሶስት ጊዜ ክፍያ የምገዛው ?…አሹቅ እየበላሁ ነው ….መኪና የማማርጠው? ….አሹቅ እየበላሁ ነው ዱባይ ያለ ምግብ ቤት የምዝናናው? …. አሹቅ እየበላሁ ነው ባለምናምን ኮከብ ሆቴል የምዝናናው ?… አሹቅ እየበላሁ ነው ለቴሌቶን ሚሊየን ብር የማዋጣው?
‹‹ፍሪጅ ከሌለዎት ምኑን ኖርኩት ይላሉ ›› የምባለው ፍሪጁን አሹቅ እንዳስቀምጥበት ነው ??…..ለምን ስራችን እና ስብከታችን ዬቅል ይሆናል ….በእርግጥ ስደት አስቀያሚ ነው ….ግን አገር ላይ በድህነት እንደመገፋት የባሰ አሰቃቂ ነገር የለም ! ሚሊየኖች በቤት ኪራይ ችግር በተንገሸገሹበት ሰዓት … እልፎች በስራ አጥነት ችግር ድግሪያቸውን እንደዣንጥላ እራሳቸው ላይ አድርገው በየማስታወቂያ ሰሌዳው ስር በሚንከራተቱባት ሰዓት ‹‹ጠግባችሁ ተሰደዳችሁ ›› ማለት …ሌላ እርድ ነው ! እንደው እነዚህ ወገኖቻችን በግላጭ በአደባባይ በግፍ ሲገደሉ አየን እንጅ በየጓዳው ስንቱ ነው የተራዘመ የችግር ሞት የሚሞተው ?! አሁንም ደላላ መርገም ስደተኛውን ተቀፅላ ስም እየለጠፉ ማሸማቀቅ መፍትሔ አይሆንም ….ፍትሃዊ የሃብት ክፍፍል ….ለህዝቡ እንደልፋቱ የሚከፈልበት ስርዓት …. ሙስናን የሚፀየፍ አስተዳደር …. እናም ጠንካራ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲና አፈፃፀም ያስፈልገናል ! ‹‹አህያውን ፈርተን ዳውላውን ››አይነት ከንቱ ልፈፋ የትም አያደርስም ! ህይዎት ብዙ መሻት ብዙ የማይገደብ ፍላጎት አላት …..ሰው በአሹቅ ብቻ አይኖርም!





Tuesday, 28 April 2015

ወይ ይች ሀገር!!

ወይ ይች ሀገር!!
ሼህ መሀመድ ሁሴን አል አሙዲን ለክሊንተን ፋውንዴሽን በ2006 ዓመተ ምህረት 20 ሚሊዮን ዶላር መስጠታቸውን ፒተር ስዋይዘር የተባሉ ጸሀፊ በቅርቡ ለህተመት በሚያበቁት መጽሀፋቸው ላይ በይፋ አጋልጠዋል። (እንኳን 20 ለምን 200 ሚሊዮን ዶላር አይሰጣቸውም? ብለን ዝም እንዳንል፤ ስጦታው የተሰጠው በኢትዮጵያ መንግስት ስም መሆኑ ያማል።ይህንንም አል አሙዲ -ለፋውንዴሽኑ በጻፉት ደብዳቤ አረጋግጠዋል። ለምን በኢትዮጵያ መንግስት ስም ሰጡ? የስጦታው ምክንያት ምንድነው?የሚል ጥያቄ ከተነሳ፤ አል አሙዲ በዚያው በስጦታ ደብዳቤያቸው ላይ ፦የቡሽ አስተዳደር የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ-በክሊንተን ጊዜም ሳይቀየር እንዲቀጥል መማጸናቸው(መጠየቃቸው)ተመልክቷል።
ያንንም ተከትሎ በባለቤታቸው ስም ገንዘቡን የተቀበሉት የወቅቱ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሄላሪ ክሊንተን የአሜሪካ መንግስት በኢህአዴግ ላይ ማእቀብ እንዲጣል ያረቀቀው አዋጅ እንዲሰረዝ ፣ ይልቁንም አሜሪካ ለኢህአዴግ አስፈላጊውን እርዳታ እንድትሰጥ ማስደረጋቸውን ደራሲው አጋልጠዋል።
(እየተዛቀ የሚወጣው የሻኪሶ (የሀገሬ)ወርቅ፤ ሀገሬን ለማፈን እንደሚውል መስማት እንዴት ያማል!!!)
“ኢህአዴግ እንድሆን ያጠመቀኝ አሰፋ ማሞ ነው” አል-አሙዲ
ለማንኛውም ይህ የአል አሙዲን እና የክሊንተን ጉዳይ በፎክስ ኒውስ ሰፊ ሽፋን ያገኘ ወቅታዊ አጀንዳ ሆኗል። ሊንኩ ከታች አለ፤ ያዳምጡት፦ አረዳው ፎክስ ኒውስ ትልቅ አጀንዳ ነው የሰጠህ። ለጊዜው እገሊትና እገሌን ተዋቸውና ይህን ጉዳይ ተወያይበት፣ተነጋገርበት..ከዚህ (ከሀገር)የሚበልጥ አጀንዳ የለም።
http://www.realclearpolitics.com/…/fox_news_special_the_tan…


ስንታየሁ ቸኮል በደህንነቶች ታፈነ!

ስንታየሁ ቸኮል በደህንነቶች ታፈነ
የቀድሞው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ የነበረው እና በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ዛሬ ሚያዝያ 20/2007 ዓ.ም በደህንነቶች ታፍኖ ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዱን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ላይ አራት ሲቪል የለበሱ ደህንነቶች ‹‹ትፈለጋለህ!›› በማለት በመኪና አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ የወሰዱት ሲሆን ለእስሩ ምንም አይነት ምክንያት ወይንም መጥሪያ እንዳልሰጡት ምንጮቻችን ገልጸውልናል፡፡ ቤቱን የፈተሹት አራቱ ደህንነቶች ምክንያታቸውን እንዲያስረዱት የጠየቀው አቶ ስንታየሁ ላይም ከፍተኛ ድብደባ እንደፈፀሙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ መንግስት የከፈተበትን የጥላቻ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲያቆም አሳሰበ

ሰማያዊ ፓርቲ መንግስት የከፈተበትን የጥላቻ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲያቆም አሳሰበ
April 27, 2015
Semayawi Parties latest press conferenceመንግስት ሊቢያ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ አሰቃቂ እርምጃ የወሰደውን አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም ራሱ በጠራው ሰልፍ ላይ ከህዝብ የገጠመውን ተቃውሞ ተከትሎ ሰማያዊ ላይ የጥላቻ ዘመቻ እንደከፈተበትና ይህንን የጥላቻ ዘመቻውን እንዲያቆም ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳስቧል፡፡Semayawi Parties latest press conference
መንግስት የጠራውን ሰልፍ ከማንም ተቃዋሚ ፓርቲ ቀድሞ የደገፈው ሰማያዊ እንደሆነ የገለጸው መግለጫው ‹‹የዜጎችን ስቃይ ለፖለቲካ ፍጆታ ማዋል የፈለገው ህወሓት/ኢህአዴግ ሰማያዊ ፓርቲ በወገኖቻችን ላይ ለሚደርሰው በደል መፍትሄ እንዲሰጥ መወትወቱ፣ የፖለቲካ ልዩነታችንን ወደ ጎን አድርገን በሰልፉ ላይ መገኘታችን እንዳላስደሰተው ከሰልፉ ቀን ጀምሮ በፓርቲያችን ላይ የተከፈተው ዘመቻ ትልቅ ማሳያ ነው፡፡›› ብሏል፡፡
ከሰልፉ ማብቃት ጀምሮም ጉዳዩን ገና ፖሊስ ሳይመረምረው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት ሚኒስትር ሬድዋን ሁሴን ሰማያዊ ፓርቲ ሁከትና ብጥብጥ ለማስነሳት እየጣረ ነው በሚል መወንጀላቸውን፣ የመንግስት ሚዲያዎች ሰማያዊ ፓርቲ ሁከትና ብጥብጥ ሊያስነሳ ነው ብለው ሚዛናዊ ያልሆነ መረጃ ማሰራጨታቸውንና አይ ኤስ አይ ኤስን ለመቃወም ተብለው በተጠሩ ሰልፎችም ሁሉ መንግስት ሰማያዊ ፓርቲ ለመቃወም እየተጠቀመባቸው መሆኑን መግለጫው አትቷል፡፡
በተጨማሪም በሰልፉ ዕለት የሰማያዊ አባላት ገና ሰልፉ ሳይጀመርና መስቀል አደባባይ ሳይደርሱ እንዲሁም ሰልፉ ካበቃ በኋላ እየታደኑ ሲታሰሩ መስቀል አደባባይ ላይ የተያዙት የኢህአዴግ አባላት ከቀበሌ ደብዳቤ እያመጡ መፈታታቸው መንግስት ሰማያዊን በሀሰት ለመወንጀል መነሳቱን ያሳያል ብሏል፡፡ በሌላ በኩል 6 ያህል የሰማያዊ አባላት በታሰሩበት ሁኔታ መንግስት 7 አመራሮችና 20 ያህል አባላት ታስረዋል ማለቱ ትክክል አለመሆኑንና ከመጀመሪያውም 6 አባላቱ የታሰሩበት መንገድና አሁንም በሰማያዊ ላይ የሚቀርበው ክስ መሰረተ ቢስ ነው ብሎታል፡፡
‹‹ይህ በህወሓት/ኢህአዴግ መንግስት አማካኝነት እየቀረበ ያለው ክስ እና የሀሰት ፕሮፓጋንዳ ህወሓት/ኢህአዴግ ለዜጎች ህይወት የማይጨነቅ እና በዜጎች ሞት የራሱን የፖለቲካ ትርፍ ለማጋበስ እና ጠንካራ ተቃዋሚ የሆነውን ሰማያዊ ፓርቲን ለማጥቃት እየተጠቀመበት መሆኑን በተጨባጭ የሚያሳይ ነው፡፡›› ሲልም የመንግስትን ተግባር ተቃውሟል፡፡ በፍርድ ቤት ውሳኔ ያልተሰጠበትን ጉዳይ ተጠርጣሪ ከማለት ይልቅ ወንጀለኞች ናቸው በማለት በህገወጥ ስራ እንደተሰማራ ያሳያል ሲልም ወቅሷል፡፡
‹‹መንግስት እና የመንግስት መገናኛ ብዙሀን ከዚህ አኩይ ተግባራቸው የማይታቀቡ ከሆነ፣ የሰማያዊን ስም በሀሰት በማጠልሸት ስራ ላይ የተሰማሩ የመንግስት ተቋማትን እና ግለሰቦችን በህግ ፊት ለማቆም ይገደዳል›› ያለው መግለጫው ሌሎች ተከታታይነት ያላቸውን እርምጃዎችም እንደሚወስድና መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሰማያዊ ፓርቲ ለሚያደርጋቸው ህዝባዊ ጥሪዎች በንቃት ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ ጥሪውን አቅርቧል፡፡

በአማራ ክልል ብቻ እሚካሄድ ሰሞኑኛ ወንጀል

በአማራ ክልል ብቻ እሚካሄድ ሰሞኑኛ ወንጀል 

በአማራ ክልል አሁንም ትጥቅ የማስፈታቱ ሂደት እንደቀጠለ ነው። የወያኔ ሎሌዎች በየገጠሩ እየዞሩ አማራውን ጠመንጃችሁን ካላስመዘገባችሁ ማዳበሪያ አታገኙም እያሉ በማስፈራራት አማሮች ሳይወዱ በግድ ጠብመንጃቸውን እያስመዘገቡ ይገኛሉ። ያስቸግራሉ የተባሉትን ደግሞ እየተቀሙ ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው። ይህም እየተደረገ ያለው ሁለት ነገር ነው፤ 
1- እንደተለመደው ወያኔ ለአማራው ባለው የማይለውጥ ጥላቻና ንቀት የተነሳና ፤
2- ኮሽ ባለች ጊዜ የተመዘገበውን ጠብመንጃ በየቤቱ ለመልቀም ያመቸው ዘንድ ነው። ወያኔ ሌት ተቀን እንደሚደሰኩረው መልካም አስተዳደርና ዲሞክራሲ ካሰፈነ፡ አማራውን ለምን ጠመንጃውን ይቀማል? በትግራይ ህዝብ ላይ የማያደርገውን በአማራው ህዝብ ላይ የመሳሪያ መቀማትና የትጥቅ ማስፈታት ያለምክንያት አይደለም “ጅብ ቀን ቀን የምትደበቀው ለምንድነው ሲሉት፡ ሌሊት ሌሊት የምሰራውን ስለማውቅ ነው” እንዳለው ሁኖበት እንጂ። እና በአማራው ህዝብ ላይ ወያኔ እየሰራው ያለው ጉድ ወይንም ወንጀል እንዳለ ከዚህ በላይ ምን ይኖራል? በነገራችን ላይ ይሄ መሳሪያ ማስፈታት ገንዘብ የሚያስገባ መሆኑም መዘንጋት የለበትም። ከሁሉም የሚያበሳጨው ግን ለህዝብና ለሀገር ሲል አጥንቱን የከሰከሰን፥ ደሙን ያፈሰሰንና እንደጧፍ የነደደት ህዝብ ማክበር ሲገባ፡ በነፍጠኝነትና በጠላትነት ተፈርጆ ማንም እየተነሳ ሲገድለው፤ ሲሰድበው፤ ሲያንኳስሰውና ሲዘለፈው ቆሞ የሚያይ አማራ ሲገኝ ነው። አማራው ዛሬ ማንም ጎጠኛ እየተነሳ አፉን ሊያፍታታበት የቻለው አማራው ለራሱ ሳይኖር ለሌላው ኖሮ ሳለ አማራውን ወያኔና በወያኔ ብርና ዶላር ገፋፊነት ወረቀት የሚያበላሹ ቅጥረኞቹ ጸሀፊና ጋዜጠኛ በሉኝ ባዮች አማራውን የስህተትና የጥፋት ቋት በማድረግ ለህዝብና ለአገር ያደረገውን አንዳች ነገር እንደሌለ በመካድ ነጋ ጠባ ውንጀላን በመደርደር ዋሾ ቅጥረኛ በመሆናቸው ነው። ከነዚህ ቅጥረኞች በተጨማሪ ተማርን ብለው የአማራን ታሪክ አጣመው በምሁርነት ካባ የሚጽፉ ሆዳሞችም አልጠፉ። እነዚህም ቢሆኑ በጠላትና በፈረንጅ ትምሀርት ቤቶች ገብተው የክህደትና መሀይምነት ዶክተሮች የሆኑ ናቸው። በነገራችን ላይ ወያኔ በአማራ ላይ የሚያደርሰው ሁሉ የጸረ ኢትዮጵያ ዘመቻ አካል ነው። ይህንን ዝም ብሎ የሚያይ የአማራ ልጅ ያልታደለና የተደየነ ብቻ ነው። የወያኔው የእጅ ስራ የሆነው ብዓዴን እንደሆነ የአማራን ህዝብ ከከዱትና ከጠሉት ከራርመዋልና የአማራን ህዝብ ይታደጋሉ ብሎ መጠበቅ ፋይዳ ቢስነት ነው። ብዓዴን ስለአማራ ይሉኝታን ከገደለ ከርሟል። በዚህም የተነሳ ወያኔ ካፈጣጠሩ አንስቶ በብዓዴን ሽፋን የአማራን ህዝብ ከማጥፋት ሌላ ራሱም በቀጥታ ተሰማርቶ ህዝባችንን እየፈጀው ይገኛል። ስለዚህ መላ ያማራ ተወላጅ የሆንህ ሁሉ ቆሻሻውንም ከጫንቃህ ላይ አንሳና ተነሳ። ስለዘርህ ስትል ዛሬውኑ ስርየትንና ንጹህነትን ፈላጊ ሁን። እና በዚህ ያደቆነኝ ሰይጣን ይጨርሰኝ ባዮች በበዙበት አገራችን ውስጥ የህዝባችን መጥፋት የሚቆጭህ ወዲህ በለኝ። የተማርን ነን የምንል የአማራ ተወላጆች ደግሞ የአማራውን ሙሉና ሀቀኛውን ታሪክ እናስተምር! ሁላችንም አማራን ስለመታደግ የምንችለውን ሁሉ እናደርግ ዘንድ ጥሪ አስተላልፍላችኋልችሁ።