ስንታየሁ ቸኮል በደህንነቶች ታፈነ
የቀድሞው አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የአዲስ አበባ ከተማ የወጣቶች ጉዳይ ኃላፊ የነበረው እና በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ ስንታየሁ ቸኮል ዛሬ ሚያዝያ 20/2007 ዓ.ም በደህንነቶች ታፍኖ ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዱን ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ላይ አራት ሲቪል የለበሱ ደህንነቶች ‹‹ትፈለጋለህ!›› በማለት በመኪና አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ የወሰዱት ሲሆን ለእስሩ ምንም አይነት ምክንያት ወይንም መጥሪያ እንዳልሰጡት ምንጮቻችን ገልጸውልናል፡፡ ቤቱን የፈተሹት አራቱ ደህንነቶች ምክንያታቸውን እንዲያስረዱት የጠየቀው አቶ ስንታየሁ ላይም ከፍተኛ ድብደባ እንደፈፀሙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
ዛሬ ጠዋት 12 ሰዓት ላይ አራት ሲቪል የለበሱ ደህንነቶች ‹‹ትፈለጋለህ!›› በማለት በመኪና አፍነው ወዳልታወቀ ቦታ የወሰዱት ሲሆን ለእስሩ ምንም አይነት ምክንያት ወይንም መጥሪያ እንዳልሰጡት ምንጮቻችን ገልጸውልናል፡፡ ቤቱን የፈተሹት አራቱ ደህንነቶች ምክንያታቸውን እንዲያስረዱት የጠየቀው አቶ ስንታየሁ ላይም ከፍተኛ ድብደባ እንደፈፀሙበት ለማወቅ ተችሏል፡፡
No comments:
Post a Comment