Monday, 18 April 2016

መንግሥቱ ኃይለማርያምን እንዴት ታደንቃለህ

መንግሥቱ ኃይለማርያምን እንዴት ታደንቃለህ በማለት መከራዬን አሳዩኝ እኮ መንግሥቱ ኃይለማርያም ጨካኝ አረመኔ ነው ይሉኛል አዎ ጨካኝ ነው ግን ከማን ጋር ተወዳድሮ ነው መንግሥቱ ጨካኝ የሆነው? ኢትዮጵያ መቼ ለሕዝቡ የሚያስብ መሪ አግኝታ ነው መንግሥቱ በተለየ መልኩ ጨካኝ ሊሆን የሚችለው?
አዎ መንግሥቱ ኃይለማርያም የሰሯቸው ጥፋቶች አሉ እነዚህን ግን መርሳት የለብንም
1. መሀይምነትን ከኢትዮጵያ ለማጥፋት ባደረገው ጥረት በወቅቱ ኢትዮጵያ ለአለም ሐገራት ተምሳሌት ሆና በዛ በዘረኛ ነጮች ጭምር እውቅና አግኝታ በUnited Nation Global initiatives on Education ተሸላሚ ሆና ነበር። ይህን የሰራው መንግሥቱ ኃይለማርያም ነው።
2. ስንቱ ፊውዳል ተቆጣጥሮት የነበረውን የሰፊው የኢትዮጵያ ሕዝብን መሬት ለድሀው ህዝብ በማከፋፈል ድሀ...ውን የቤት ባለቤት ማድረግ ያስቻለው መንግሥቱ ሐይለማሪያም የሚመራው ሥርአት ነው። አዲስ አበባ የሚገኙ ሰፈሮችን እንኳ ተመልከቱ ኮተቤ እንኳን የአራት ፊውዳሎች ይዞታ ነበረች። ከእነዚህ አራት ፊውዳሎች አንዷ ወይዘሮ አመለወርቅ ትባል ነበረ ወይዘሮ አመለወርቅ ደግሞ የማን ቅምጥ እንደነበረች ወይ አንብቡ አልያም ጠይቁ
3. ግልጊቤ ቁጥር አንድና ሁለት ግድቦችን የሰራው ማነው? ኢህአዴግ ያስመረቀውን የጣና በለስ ፕሮጀክት 90 ከመቶ በላይ ያሰራው ማነው?
4. በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ወላጅ አልባ ህፃናትን ሰብስቦ ተገቢውን እንክብካቤ እየሰጠ ያሳደገውስ መሪ መንግሥቱ ኃይለማርያም አይደለምን?
5. ሀገሪቱን በሰሜን ሻእቢያ፣ ህውሀት፣ ኢዲዩ በምስራቅ ሶማልያ በማእከላዊ ኢሕአፓ እየወጓት እንኳን ህዝቡን ከችግር የጠበቀው ማነው? ሌላም ሌላም መጨመር ይቻላል
ስለመንግሥቱ ጭካኔ ስታወሩ ይህንንም መጨመር አለባችሁ አለበለዛ በጭፍን መንግሥቱ ጨካኝ ነው ስትሉ ሀይቅ ዳር ነፋሻማ መሬት ላይ በጀርባቹህ አስተኝቶ የሚቀልባቹህ መሪ ያላቹህ ነው የምትመሰሉት።
በመጨረሻም ከመንግሥቱ ስህተቶች በጣም የሚያናድደኝን ልንገራችሁ "መንግሥቱ ኤርትራን መሸጥ ነበረበት ኤርትራ ብትሸጥ ኖሮ አሁን ያለው መንግሥት አራት ኪሎ አይገባም ነበር ሆኖም ይህንን እንዳያደርግ ሰውዬው በዳር ድንበር ቀልድ አያውቅም ቀ
‪#‎ኤርሚያስ_ቶኩማ‬


Thursday, 14 April 2016

ሰበር ዜና — አቶ አንዳርጋቸዉ ጽጌ ለትግራዩ ነጻ አዉጭ ቡድን ደህንነት ቢሮ ከፍተኛ እራስ ምታት ሆኗል

 April 14, 2016 0

በልኡል አለም
የተከበሩት የቀድሞ የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ ለወያኔ በግፍ ተላለፈዉ ሲሰጡ የእንግሊዝ የደህንነት አካላት ያዉቁ እነደነበር እና የየመን የጸጥታ ሐይሎች እንዲሁም የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን በመተባበር እገታዉን እንዳካሄዱት ዛሬ ከብሔራዊ መረጃ ምንጭ ተገኝቷል።
የእንግሊዝ ከፍተኛ የደህንነት አባላትን ጨምሮ አጣብቂኝ ዉስጥ የከተቱት አንዳርጋቸዉ ጽጌ በአምነስቲ ኢንተርናሽናልና በሌሎች ሁለት ከፍተኛ ተደማጭነት ባላቸዉ የሰባዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች እንዲሁም በወላጅ አባታቸዉ የሚጎበኙ ሲሆን የተለያዩ የወያኔን ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ዲስኩር ያዘሉ መጽሐፎች፣ እና መጽሄቶች በተለይም የክቡሩን ታጋይ ሞራል በሚነካ መልኩ አንዳንድ አልባሌ ጽሁፎችን ያካተቱ መጣጥፎችም ሆን ተብለዉ እንዲሰጡት ቢደረግም በጀግናዉ አንዳርጋቸዉ ላይ እየታየ ያለዉ አልበገር ባይነት በወያኔያዊያን ላይ የበላይነቱን ይዟል።
በተልይም የደህንነት ቢሮዉ ሚስጥራዊና ልዩ ስብሰባ ያካሔደ ሲሆን የእንግሊዝ ባለስልጣናት እራሳቸዉን ከተጠያቂነት ባሸሸ መልኩ በተገላቢጦሹ ታጋይ አንዳርጋቸዉን እንድንፈታ እያስገደዱን ነዉ። “ሰባዊ መብት ጥሰቱ እስካልቆመና አንዳርጋቸዉ ጽጌ ካልተፈታ ወይም አስቸኳይ የሆነ የአቋም ለዉጥ በኢትዮጵያ በኩል እስካልተደረገ ድረስ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስቴር የኢትዮጵያ ጉብኝት እንደሚሰረዝ ማሳስጠንቀቂያ አዘል ትእዛዝ ተሰጥቶናል” በሚል አጀንዳ ተንተርሶ የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን ጭንቅ ዉስጥ ገብቷል።
እንዳይለቁት እሳት እንዳይዙት መአት!!!  ይሏል ይህ ነዉ!!
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

Monday, 11 April 2016

የኦነግ የወጣቶች ክንፍ በማደራጀት ውጊያ ሊያካሄዱ ነበር የተባሉ 33 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

በአዲስ አበባ ከተማ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የወጣቶች ክንፍን በማደራጀት ከመንግስት ጋር ውጊያን ሊያካሄዱ ነበር የተባሉ 33 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ክስ እንደተመሰረተባቸው ተዘገበ። ተጠርጣሪዎቹ በተለምዶ ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአንድ መኖሪያ ቤት የእምነት ስነስርዓት የሚያካሄዱ በመምሰል ለወጣቶች ክንፍ አባላት ሲመለምሉና ሲያደራጁ መቆየታቸውን ከሳሽ አቃቤ ህግ በክሱ አቅርቧል ሲል ሪፖርተር ገልጿል። ተጠርጣሪዎቹ መንግስት የኦሮሞን መሬት እየቆራረሰ በመሆኑ የኦሮሞ ህዝብ እጅና ጓንት በመሆን መንግስትን መዋጋት አለበት የሚል ቅስቀሳን ሲያካሄዱ መቆየታቸውንም በጠርጣሪዎቹ ላይ የቀረበን ክስ ዋቢ በማድረግ በሃገር ውስጥ ያሉ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ሃብቷሙ ሚልከሳ ጫሊ ኦና ረዳት ሳጅን ጫላ ፍቃዱ አብደታ የተባሉ ግለሰቦች የወጣቶቹ ክንፍ ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበር በመሆን እንቅስቃሴ ማካሄዳቸውንም አቃቤ ህግ በክሱ አመልክቷል። በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ቡልቡላ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ተጠርጣሪዎቹ በአንድ ግቢ ውስጥ 60 የሚሆኑ አባላትን በማሰባሰብና የኦነግን ባንዲራ እንዲይዙ በማድረግ ለድርጅቱ ለጊዜው መጠኑ ያልታወቀ ገቢ ማሰባሰባቸውንም ከሳሽ አቃቢ ህግ ባቀረበው የሽብርተኛ ክስ አስፍሯል። ባለፈው ህዳር ወር በቁጥጥር ስር ውለዋል የተባሉት ተጠርጣሪዎች ላይ የቀረበውን ክስ በመመልከት ፍርድ ቤቱ ለሚያዚያ 7 ፥ 2008 አም ቀጠሮ መስጠቱ ታውቋል። ተጠርጣሪዎቹ ከአራት ወራት በፊት በቁጥጥር ስር መዋላቸው ቢገለጽም፣ እስካሁን ድረስ ለምን ክስ እንዳልተመሰረተባቸው የታወቀ ነገር የሌለ ሲሆን፣ በቅርቡ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር በተገናኘ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ተከትሎ በርካታ ሰዎች የኦነግ አባላት ናችሁ ተብለው ለእስር መዳረጋቸውን የተለያዩ አካላት ይገልጻሉ። የመንግስት ባለስልጣናት ተቃውሞ በቁጥጥር ስር ዉሏል ቢሉም ተቃውሞው አሁንም ድረስ እልባት አለማግኘቱን ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል።

በድርቅ ለተጎዱ ዜጎች የታሰበው የዕርዳታ ማሰባሰብ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም የኢትዮጵያ መንግስት ትዕዛዝ ሰጠ

ኢትዮጵያውያን የድርቅ ተጠቂዎችን ለመታደግ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ (OCHA) ከሌሎች ለጋሾች ጋር ያስተባበረው የዕርዳታ ማሰባሰብ ዘመቻ በአስቸኳይ እንዲቆም የኢትዮጵያ መንግስት ትዕዛዝ ሰጠ። የኢሳት ምንጮች ከአዲስ አበባ እንደገለጹት ለአዲስ አበባው የኦቻ (OCHA) ተጠሪ ማሰባሰቢያውን የሰጡት የጠ/ሚኒስትሩ ልዩ መልዕከተኛ አምባሳደር ብርሃነ ገብረክርስቶስ ናቸው። 10.2 ሚሊዮን በቀጥታ በድርቁ ተጠቂ በመሆናቸው ሌሎች 8 ሚሊዮን ዜጎች ደግሞ በሶፍትኔት የታቀፉ የዕለት ድረሽ ምግብ ጠባቂ በመሆናቸው ለ18 ሚሊዮን ህዝብ ምግብ በማስፈለጉ ዓለም-አቀፍ ድርጅቶቹ እ/ኤ/አ ማርች 23/2016 የዕርዳታ ማሰባሰብ ዘመቻ መጀመራቸውም ታውቋል። ይህ በመገናኛ ብዙሃን የተጀመረው የዕርዳታ ዘመቻ የኢትዮጵያን ገጽታ ይጎዳል በሚል መንግስት እንደቆይ መወሰኑን መረዳት ተችሏል። ከ10 ቀናት በፊት እ/ኤ/አ ማርች 23/2016 ለኢትዮጵያውያን ዕርዳታ ለማሰባሰብ በፌስ ቡክ፣ ትዊተር እና በለጋሾች ዌብሳይት ዘመቻውን የጀመሩት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አካል የሆነው የሰብዓዊ ጉዳዮችን ቢሮ (OCHA) የአሜሪካ የዕርዳታ ድርጅት ዩ ኤስ ኤይድ (USAID) ሴቭ ዘ ችልድረን (SAVe The Childeren)፣ ዩኒሴፍ (UNICEF)፣ እና ሌሎች አለም አቀፍ ድርጅቶች መሆናቸውንም መረዳት ተችሏል። በተያዘው የምዕራብያውያኑ ዓመት 2016 ረሃብተኛ ኢትዮጵያውያንን ለመታደግ የሚያስፈልገው 1.4 ቢሊዮን ዶላር ባለመገኘቱ አለም-አቀፍ ተቋማቱ ዘመቻውን ከፍተዋል። የጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ልዩ መልዕክተኛ የሚል ሹመት የተሰጣቸው የቀድሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ዘመቻው እንዲቆም አሳስበው ዕርዳታውን እንዳይሰባሰብ ለኦቻ (OCHA) ዳይሬክተር መናገራቸውን ምንጮች ለኢሳት ገልጸዋል። በኢትዮጵያ የኦቻ (OCHA) ዳይሬከተር በበኩላቸው ለጋሾቹ ወደ ሚዲያ ዘመቻ ለመግባት የተገደዱበትን ሁኔታ አስረድተዋል። የድርቅ ተጎጂዎች ለመታደግ የሚያስፈልገው 1.4 ቢሊዮን ዶላር ሲሆን፣ የተገኘው ከግማሽ በታች 686 ሚሊዮን ዶላር ነው። ይህ በአለም-አቀፍ ለጋሾች በኩል የታየውን ደካማ ምላሽ ለማሸነፍ ሲባል ዘመቻው መከፈቱን አብራርተዋል። አምባሳደሩ የመንግስታቸው አቋም የማይቀየርና ዘመቻው መሰረዙ የግድ መሆኑን የገለጹ ሲሆን፣ ዕርምጃው የኢትዮጵያን መንግስት ገጽታ በአለም-አቀፍ ደረጃ ይካሄዳል በማለት ማሳሰባቸውም ተመልክቷል። በተጨማሪም ለገንዘብ ዕጥረቱ ለየትኛውም የምዕራብ ሚዲያ እንዳይሰጡም ማሳሰባቢያ ተሰጥቷቸዋል። በኢትዮጵያ የኦቻ ተወካይ ከአምባሳደር ብርሃነ ገ/ክርስቶስ ማሳሰቢያ በኋላ፣ አለም አቀፍ ደረጃ ያለው ምላሽ ደካማ መሆኑን በመግለፅ፣ ዘመቻውን ለመክፈት የተገደደበትን ሁኔታ ያስረዱ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት አለ ያሉትንም አሳሳቢ ችግር ጠቅሰዋል። በሶማሊ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ክልል ላለፉት 60 ቀናት ድጋፍ ያላገኙ ተረጂዎች መኖራቸውን የጠቀሱ ስሆን፣ አምባሳደር በቂ ምግብ ወደብ ላይ አለ፣ ችግሩ ትራስፖርት ነው ብለዋል። የተባበሩት መንግስታት የሰብዓዊ ጉዳዮች ቢሮ የኢትዮጵያ ተጠሪ ሰለባዎቹ ያሉበት አሳሳቢ ሁኔታ በሚመለከት፣ መንግስት ውሳኔውን እንደገና እንዲመረምር መማጸናቸውም ተመልክቷል። ሆኖም አምባሳደር ብርሃነ ገ/ክርስቶስ የመንግስት ውሳኔ የማይለወጥ መሆኑን አስረግጠው ካልተስማማችሁ ቢሯችሁን ዘግታችሁ መውጣት ትችላላችሁ ሲሉ ማሳሰባቸውን ለኢሳት በዝርዘር የደረሰው መረጃ ያሳያል። 10.2 ሚልዮን የድርቅ ተጠቂዎችን እንዲሁም በሶፍት ኔት የታቀፉ 8 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን በአጠቃላይ 18.2 ሚሊዮን ዜጎች ለመታደግ ማርች 23/2016 የተጀመረው ዘመቻ የመንግስትን ማሳሰብያ ተከትሎ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ተቋርጧል። ዘመቻው የተከፈተው ለ90 ቀናት እንደነበርም ታውቋል።

በጣሊያኑዋ በቶሪኖ የተጠራው የመንግስት ስብሰባ በተቃውሞ ተበተነ

እሁድ ሚያዚያ 3፣ 2008 ዓም በጣሊያኑዋ የቶሪኖ ከተማ መንግስት ለአባይ ግድብ ማሰሪያ ቦንድ ለመጨጥ እንዲሁም አወዛጋቢ የሆነውን የኮንዶሚኒየም ሽያጭ ለማከናወን እና የውጭ ምንዛሬ ለመሰብሰብ የጠራው ስብሰባ በከተማዋ በሚገኙ ኢትጵያውያን ተቃውሞ እንዲሰረዝ ተደርጎአል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ገና ከመነሻው ተቃውሞአቸውን ያሰሙ ሲሆን፣ መሰረታዊ የሚባሉ የመብት፣ የእኩልነትና የኢኮኖሚ አስተዳደር ጥያቄዎችን አንስተው ተቃውአቸውን አሰምተዋል፡፡ አንድ አራተኛው የኢትዮጵያ ህዝብ በተራበበት ሁኔታ፣ ቅድሚያ የሰዎችን ህይወት መታደግ ሲገባችሁ እናንተ ግን የት እንደምታደርሱት ለማይታቅ ገንዘብ ለመሰብሰብ አጀንዳ ከፈታችሁ፤ ይሄ ከአገርም በላይ ሰብአዊነትን የሚመለከት በመሆኑ ቅድሚያ ለሰው ልጅ ህይወት ስጡ ያሉት ዜጎች፣ ከ300 በላይ የኦሮሞ ወገኖች ባለቁበት ሰአት፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ታስረው በሚሰቃዩበት በዚህ ወቅት፣ እንዲሁም በወልቃይት ጥያቄ ዙሪያ ዜጎች ስቃያቸውን እያዩ፣ እናንተ ምንም ሳይመስላችሁ፣ ስለ ውጭ ምንዛሬ ልትነግሩን አጀንዳ ከፈታችሁ፣ ይሄ ያሳፍራል ሲሉ በምሬት ትቃውአቸውን ገልጸዋል፡፡ በውጭ ለሚገኘው ዜጋ ቤት ከመጨነቃችሁ በፊት በቅድሚያ ቤት አጥቶ ለሚሰቃየው አገር ቤት ላለው ህዝብ ቤት ስሩለት በማለት፣ በአገር ቤት ህዝብ ቤት አጥቶ እየተሰቃዬ፣ በተሻለ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኘው በውጭ ለሚገኘው ዜጋ ቤት ለመስጠት የሚደረገውን ሩጫ በአስመሳይነት በመፈረጅ አውግዘዋል ኢትዮጵያውያኑበአገሪቱ ውስጥ የአንድ ብሄር የበላይነት መኖሩን፣ እንዲሁም ከ20 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ተርቦ እናንተ ኢሳትን ለማፈን ከፍተኛ ገንዘብ ታወጣላችሁ በማለት የሞራል ጥያቄ አንስተው ተቃውመዋል፡፡ አገሩን ለቀን ወጣንላቸው ፣ እዚህ ደግሞ ገንዘባችንን ፡፡ ሊወስዱ ይመጣሉ በማለት ተቃውሞአቸውን በማሰማት መንግስት ስብሰባውን ለመሰረዝ ተገዱዋል፡፡ በፊላደልፊያም ተመሳሳይ ተቃውሞ መደረጉ ታውቆአል፡፡

የሶስት ኢትዮጵያውያን ንብረት ነው የተባለ 356 ሺ ዶላር በቻይና የጉአንግዙ መገኘቱን የቻይና መገናኛ ብዙሃን ዘገቡ

በቻይና የጉአንግዙ ግዛት በሚገኝ አንድ አለም-አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ የሶስት ኢትዮጵያውያን ንብረት ነው የተባለ 356 ሺ ጥሬ ዶላር መገኘቱን የቻይና መገናኛ ብዙሃን ሰኞ ዘገቡ። በአንድ ሻንጣ ተሞልቶ የነበረው ይኸው ከፍተኛ ገንዘብ በአየር መንገዱ መሳፈሪያ አካባቢ ለጉዞ በነበሩ ሁለት የኮንስትራክሽን ሰራተኞች መገኘቱንና የንብረቱ ባለቤት ናቸው ለተባሉት ሶስቱ ኢትዮጵያውያን መሰጠቱ ታውቋል። 356ሺ ጥሬ ዶላር ገንዘብን የያዘው አነስተኛ ሻንጣ በዋናው የአየር ማረፊያው መግቢያ ላይ መገኘቱንና ሁለቱ ግለሰቦች ለፖሊስ ማስረከባቸውን የቻይናው ዜና አገልግሎት ዢንሁዋ ሰኞ ዘግቧል። የሻንጣው ባለቤት አድራሻ ለማግኘት በማሰብ ሁለቱ ቻይናውያን ሻንጣውን ቢፈቱም አይተውት የማያውቁት ገንዘብን በሻንጣው በማየታቸው ድንጋጤ እንዳደረባቸውና ገንዘቡን ለፖሊስ እንዳስረከቡ ቻይናውያኑ አስረድተዋል። ገንዘቡን የቆጠሩት የቻይና የጸጥታ ሃይሎችም የገንዘቡ ባለቤት ናቸው ለተባሉ ሶስቱ ኢትዮጵያውያን ያስረከቡ ሲሆን፣ የሶስቱ ኢትዮጵያውያን ማንነት ግን ይፋ አልተደረገም። ይህን ያህል መጠን ያለው ገንዘብ በበርካታ ሃገራት በጥሬ ይዞ መንቀሳቀስ የማይፈቀድ ቢሆንም፣ የቻይና የጸጥታ ሃይሎች ግን በዚህ ጉዳይ ዙሪያ የሰጡት ዝርዝር የለም። የባለ መቶ ኖቶቹን 356ሺህ ሶላር (ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ) የያዙት ኢትዮጵያውያን ገንዘቡን ለምን ጉዳይ እንደያዙትና ለምን አላማ ሊያዉሉት እንደነበርም የቻይና ፖሊሶች የሰጡት ዝርዝር መረጃ የለም። የኢትዮጵያ አየር መንገድ በሳምንት ሶስት ቀን ወደ ቻይናው ጓንጉዙ አየር ማረፊያ በረራን እንደሚያደርግ ለመረዳት ተችሏል። ከወራት በፊት በአውሮፕላን እቃ መጫኛ ክፍል ውስጥ ተደብቆ ስዊድን ሃገር ከገባ በኋላ በሃገሪቱ የፖለቲካ ጥገኝነትን የጠየቀ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ በመንግስት ባለስልጣናት ዶላር በሻንጣ እየተደረገ እንደሚወጣ ለኢሳት መግለጹ ይታወሳል። ከኢትዮጵያ ጋር የቅርብ ወዳጅነት አላት በምትባለው ቻይና በርካታ በለስልጣናት ለተለያዩ ጉዳዮች በየጊዜው እንደሚጓዙባትም ይነገራል።

Friday, 8 April 2016

በኢትዮጵያ የፌዴራሊዝም ስርዓት አተገባበር ጥያቄ እንዳስነሳ የብሪታኒያው ዘ-ጋሪድያን ዘገበ

 በኢትዮጵያ የፖለቲካ ልዩነቶችንና አመለካከቶችን በተገቢው ሁኔታ ሊስተናገዱ ባለመቻላቸው በሃገሪቱ ተቃውሞ ኣየተባበሱ መምጣቱን የብሪታኒያው ዘ-ጋሪድያን ጋዜጣ የተለያዩ መረጃዎች ዋቢ በማድረግ አርብ ዘገበ። በተለያዩ ክልሎች መጠኑን እያሰፋ የመጣው ይኸው ተቃዎሞ በኢትዮጵያ የፌዴራሊዝም ስርዓት አተገባበርና በዴሞክራሲያዊ የመብት ጥያቄዎች ላይ ጥያቄ አስነስቶ እንደሚገኝም ጋዜጣው አስነብቧል። በኦሮሚያ ክልል በተቀሰቀሰው ተቃውሞ በትንሹ 266 ሰዎች በጸጥታ ሃይሎች መገደላቸውን ያወሳው ጋዜጣው አስተዳደራዊ ጥያቄን ባነሱ የኮንሶ ማህበረሰብ ዘንድም የሃይል እርምጃ መወሰዱን አመልክቷል። የሃገሪቱን የብሄር ብሄረሰቦች መብት በመጠቀም በደቡብ ክልል የተነሳውን ይህንኑ ጥያቄ ተከትሎ የኮንሶ ማህበረሰብ መሪ የሆኑን ካላ ገዛኸኝ በቁጥጥር ስር ውለው እንደነበረም ዘ-ጋርዲያን ጋዜጣ በዘገባው አውስቷል። በአማራ ክልል ከቅማት ማህበረሰብ የአስተዳደር ጥያቄ ጋር በተያያዘ ለአመታት የቆየ ተቃውሞ ሲሰማ መቆየቱን የዘገበው ጋዜጣው በሃገሪቱ የፖለቲካ አመለካከቶችና ልዩነቶች በአግባቡ ሊስተናገዱ ባለመቻላቸው በመንግስት ላይ የሚነሱ ተቃውሞዎች እየተባባሱ መምጣታቸውን አስነብቧል። በኢትዮጵያ ተግባራዊ ተደርጎ የሚገኘውንና ብሄርን ማዕከል ያደረገው የፌዴራሊዝም ስርዓትም የተጠበቀውን ያህል መረጋጋትና ዘላቂ ሰላም ሊያመጣ እንደማይችልም በጉዳዩ ዙሪያ የሚሰሩ አካላት ገልጸዋል። የፌዴራል መንግስት በክልሎች ሊያካሄድ ባሰበው የኢኮኖሚና ተዛማች ጉዳዮች ዙሪያ ከህብረተሰቡ ጋር ምክክሮችን ማካሄድ ቢጠበቀበትም እየሆነ ያለው ግን የዚህ ተቃራኒ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የፌዴራሊም ባለሙያ የሆኑት አቶ አሰፋ ፍሰሃ ለዘ-ጋርዲያን ጋዜጣ አስረድተዋል። የፌዴራል መንግስት ክልሎችን ሳያማክር ሰፋፊ የስኳር ፋብሪካዎችንና ሌሎች ፕሮጄክቶችንም በራሱ ስልጣን እያከናወነ እንደሚገኝ ጋዜጣው የተለያዩ መረጃዎች በምሳሌነት በማቅረብ ዘግቧል። ገዢው የኢህአዴግ መንግስት በቅርቡ በተካሄደው ብሄራዊ ምርጫ መቶ በመቶ ማሸነፉን ያወሳው ጋዜጣው ውጤቱን ተከትሎ መቀስቀስ የጀመረው ተቃውሞ በፓርቲው የበላይነት ላይ ችግሮች እየገጠሙት እንደሆነ ማሳያ ነው ሲል ዘ-ጋርዲያን ጋዜጣ በዘገባው አስፍሯል። በሃገሪቱ ያለው የፌዴራል ስርዓትም ከተለያዩ አካላት ዘንድ ጥያቄ እየቀረበበት እንደሚገኝም ጋዜጣው አክሎ ዘግቧል።

ጋዜጠኛ አበበ ገላው የኢሳት አለም-አቀፍ ዳይሬክተር ሆኖ ተሾመ

የኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ቦርድ ለኢሳት አለም-አቀፍ አዲስ ዳይሬክተር መሾሙን ይፋ አደረገ። የቀድሞውን የኢሳት አለም አቀፍ ዳይሬክተር አቶ ነዓምን ዘለቀ በክብርና በምስጋና የሸኘው የኢሳት ቦርድ ጋዜጠኛ አበበ ገላው የኢሳት አለም አቀፍ ዳይሬክተር እንደሆነ ከኤፕሪል 1 ፥ 2016 ጀምሮ መሾሙን አስታውቋል። 
በአሁኑ ወቅት በካሊፎርኒያ ግዛት ሲልከን ቫሊ የሚገኘው ጋዜጠኛ አበበ ገላው ከኢሳት አስተዳደር ቦርድ በተሰጠው ሹመት መሰረት በቀጣዩ ሳምንት ወደ ዋሽንግተን በመምጣት ሙሉ ጊዜውን በኢሳት ውስጥ እንደሚሰራም ለመረዳት ተችሏል። እኤአ ከ2011 ጀምሮ እስከ 2013 በኢሳት ውስጥ ሲያገለግል የነበረው ጋዜጠና አበበ ገላው፣ ላለፉት 3 ሳምንታት ካሊፎርኒያ ግዛት ሲልከንቫሊ በሚገኝ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ኩባንያ ውስጥ ሲሰራ ቆይቷል። የኢሳት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ነዓምን ዘለቀ ሙሉ ጊዚያቸውን በኢሳት ውስጥ ለማሳለፍ በስራ መደራረብ ሳቢያ ባለመቻላቸው አዲስ ዳይሬክተር ሲያፈላልግ የቆየው የኢሳት ቦርድ ጋዜጠኛ አበበ ገላው ከተገመገሙ ዕጩዎች ውስጥ ለቦታው ብቁ ሆኖ በመገኘቱ በዳይሬክተርነት መሾሙን አስታውቀዋል። ቦርዱ ኢሳትን በዳይሬክተርነት ለረጅም ዓመታት ለመሩት ለአቶ ነዓምን ዘለቀ እንዲሁም ካለበት ተደራራቢ ሃላፊነቶች በተጨማሪ የኢሳትን ዳይሬክተርነት በተጠባባቂነት ለወራት ሲመራ ለቆየው ለአክቲቪስት ታማኝ በየነ ምስጋናውን አቅርቧል።

Thursday, 7 April 2016

በ2016 በድርቅ እና በጎርፍ አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ ተመድ ገለጸ

በተያዘው የፈረንጆች አመት (2016) ወደ አንድ ሚሊዮን የሚጠጉ ሰዎች በኢትዮጵያ ተከስቶ ባለው የድርቅ አደጋ ሊፈናቀሉ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ገለጠ። ድርቁ እያደረሰ ካለው ጉዳት በተጨማሪ የጎርፍ አደጋም ለሰዎቹ መፈናቀል ምክንያት ሊሆን እንደሚችል ድርጅቱ በወቅታዊው የኢትዮጵያ የድርቅ ሁኔታ ዙሪያ በወጣው ሪፖርት አመልክቷል። አሁን በሃገሪቱ ተከስቶ ካለው የድርቅ አደጋ አንጻርም በቂ የህክምና አገልግሎቶች ተሟልተው አለመገኘታቸውን የገለጸው ድርጅቱ በድርቁና በጎርፍ አደጋ የሚከሰተው ጥፋትም የበርካታ ሰዎችን ህይወት ሊቀጥፍ እንደሚችልም አሳስቧል። በድርቅ በተጎዱ አካባቢዎችም የወባ በሽታን ጨምሮ ህጻናትን በአጣዳፊ የሚገድሉ ተላላፊ በሽታዎች በወረርሽኝ መልክ ሊከሰቱ እንደሚችሉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አክሎ ገልጿል። በድርቁ ሳቢያ በተፈጠረው የምግብ ኣጥረት ክፉኛ የአካልና የጤና ጉዳት ደርሶባቸው የሚገኙ ወደ ግማሽ ሚሊዮን ህጻናትም እየተባባሰ በሚሄደው የድርቅ አደጋ ያልተጠበቀ አደጋ ሊገጥማቸው እንደሚችል የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል። ወደ ሁለት ሚሊዮን አካባቢ የሚደርሱና በምግብ እጥረት ላይ የሚገኙ እርጉዝ እናቶችም በምግብ እጥረቱ ምክንያት እርግናቸው ሊጨናገፍ እንደሚችል ድርጅቱ አሳስቧል። ለተረጂዎች የሚደርስ የእህል እርዳታ በጅቡቲ ወደብ ቢደርስም በወደቡ የተፈጠረ መጨናነቅ የእርዳታ እህሉ ለተረጂዎች በወቅቱ እንዳይደርስ ታውቋል። የጫኑትን የእህል አቅርቦት ማውረድ ያልቻሉ ከ10 በላይ መርከቦችም ወደሱዳንና ሶማሊላንድ በርበራ ወደብ እያቀኑ መሆናቸውን የመንግስት ባለስልጣናት መግለጻቸው ይታወሳል። ለአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ከተጋለጡት ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች መካከልም 3.6 ሚሊዮን የሚሆኑት የህክምና ድጋፍን የሚፈልጉ እንደሆነ ታውቋል። በስድስት ክልሎች ተከትስቶ ያለው የድርቅ አደጋ መባባስን ተከትሎ ወደ ረሃብ ደረጃ ሊደርሱ ይችላሉ የሚባሉ ወረዳዎች ቁጥርም ኣየጨመረ መምጣቱን የእርዳታ ተቋማት በመግለጽ ላይ ናቸው። ሰሞኑን በጅጅጋ ከተማ በደረሰ የጎርፍ አደጋ ከ20 በላይ ሰዎች መሞታቸውንና ከ50 የሚበጡ ደግሞ የገቡበት አለመታወቁ መገለጹም ይታወሳል።

በአማራው ክልል ፕሬዚዳንት ላይ ያነጣጠረ ግምገማ እየተካሄደ ነው

በቅርቡ በአማራ ክልል ተነስተው የነበሩትንና እስካሁንም መቁዋጫ ያልተገኘላቸውን የቅማንትና የወልቃይት ጠገዴን ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄን ተከትሎ ለደረሰው ደም መፋሰስ የክልሉን ፕሬዚዳንት አቶ ገዱ አንዳጋቸውን ተጠያቂ በማድግ የህዝቡን ጥያቄ ለማፈን በመሩዋሩዋጥ ላይ መሆኑን ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ወገኖች ገልጸዋል፡፡ የወልቃይት ጥያቄ የአቶ ገዱ የአመራር ችግር እንጅ የአማራ ህዝብ ጥያቄ አይደለም በሚል፣ ፕሬዚዳንቱን ከብአዴን አባላት እና ከህዝቡ ጋር በማጋጨት፣ ጥያቄው ተዳፍኖ እንዲቀር ለማድረግ ጥረት እየተደረገ መሆኑን እነዚህ ወገኖች ይገልጻሉ፡፡ ከመጋቢት 23 ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት በሁሉም ዞኖች ሲካሄድ በሰነበተው የብአዴን የህዋስ ግምገማ ፣ ሁለት አላማዎችን ለማሳካት መታቀዱን የሚገልጹት ታዛቢዎች፣ አንደኛው፣ የአማራ መብት አልተጠበቀም፣ አማራ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገባውን ቦታ አላገኘም፣ የወልቃይት ጠገዴ፣ የሱዳን መሬትና ሌሎችም ተያያዝ ጥያቄ ያነሱ የድርጅቱን አባላት፣ በጠባነትና በተቃዋሚ አጀንዳ አራማጅነት በመክሰስ ነጥሎ ለመምታ ሲሆን፣ ሌላው ደግሞ የወልቃይት ጠገዴን ጥያቄ የአቶ ገዱ አንዳርጋቸው የግል አጀንዳ በተለይም ከትግራይ ክልል መሪ ከአቶ አባይ ወልዱ ጋር ባላቸው ቅራኔ የተነሳ የተፈጠረ ነው በሚል፣ጥያቄዉን ግልሰባዊ ይዘት በመስጠት፣ ህዝባዊነቱን መንጠቅ የሚል ነው፡፡ በዚህም መሰረት፣ በግምገማው ወቅት፣ የህዝብ ጥያቄዎች ናቸው በሚል የተለያዩ ጥያቄዎችን ሲያነሱ በነበሩ የብአዴን አባላት ላይ በየመድረኩ የማሸማቀቅና የማስፈራራት ስራ በመስራት አንገታቸውን እንዲደፉ ተደርጎአል፡፡ በእነዚህ አባላት ላይ በሂደት እርምጃ ሊወሰድ እንደሚችልም ታዛቢዎች ይገልጻሉ፡፡ በሌላ በኩል ሆን ተብሎ በህወሃት የደህንነት አባላት እና ለህወሃት ታማኝነተን አላቸው በሚባሉ የብአዴን አባላት በተቀነባረው ስብሰባ አቶ ገዱን በስም እየጠቀሱ፣ የወልቃይት ችግር የግለሰብ ችግር መሆኑን ለማሳየት ጥረት ተደርጎአል፡፡ በግምገማዎች ላይ ሁሉ የሁለቱ ክልሎች መሬዎች ስም ሲነሳ የቆየ ሲሆን፣ የአቶ አባይ ስም እንዲጠራ የተፈለገው፣ አባላቱን ለማሳመንና ጉዳዩ ሴራ ያለበት እንዳይመስል ነው ይላሉ፡፡ የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ማንነት ጥያቄ የህዝብ ጥያቄ ሳይሆን የግለሰብ መሪዎች ጥያቄ ነው በማለት፣ ብአዴን ጥያቄው እንደማይመለከተውና ችግሩን የፈጠሩት መሪዎች መሆናቸውን በማሳየት፣ ጥያቄው ተዳፍኖ እንዲቀር ጥረት በመደረግ ላይ ነው፡፡ የግምገማ ውጤቱ በሂደት የሚታይ ቢሆንም፣ የወልቃይት ጥያቄ እየገፋ የሚሄድ ከሆነ፣ አቶ ገዱን በማንሳት ጥያቄውን ለማዳፈን ሙከራ ለደረግ ይችላል፡፡ በዚህ ግምገማ ላይ የወልቃይት ህወሃት የወልቃይትን ጥያቄ የግለሰብ ጥያቄ አድርጎ በማቅረብ ለማዳፈን እየሄደበት ያለው ርቀት ችግሩን እንደማይፈታው ይናገራሉ፡፡ አብዛኛው የብአዴን መካከለኛና ተራ አባላት ብአዴን 25 አመታት ሙሉ የህወሃት ታዛዥ መሆኑን የሚቃወሙ ሲሆን፣ ሰሞኑን በተካደው ግምገማም ይህ ተቃውሞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ከፍ ብሎ ተሰምቶአል፡፡ ከህወሃት ጋር ቅርብ ግንኙነት አላቸው የሚባሉት የብአዴን ከፍተኛ መሪዎች፣ ታች ያለው አባሉ እያነሳ ያለውን ጥያቄ የማደግፉና በጥርጣሬ የሚመለከቱ ናቸው፡፡ ከፍተኛ አመራሩ እርስ በርስ ለስልጣን በሚያደርጉት ፉክክር፣ አንዱ ሌላውን አሳልፎ እየሰጠ መሆኑን ታዛቢዎች አክለዋል፡፡ በሌላ በኩል የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከህወሃት ጋር በእየለቱ ግጭት ውስጥ እየገባ መሆኑን ከአካባቢው የሚደርሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የህወሃት ካድሬዎች የወልቃይትን የአማራ ማንነት ይደግፋሉ የሚሉዋቸውን እየተከታተሉ በማስፈራራት ላይ ሲሆኑ፣ በህዝቡ መካከል ግጭት ለመፍጠር የሚደረገው ጥረት አካባቢውን አስፈሪ አድርጎታል፡፡ ህወሃት ጥያቄውን ለመመለስ እየተከተለው ያለው መንገድ አካባቢውን ወደ እርስ በርስ ግጭት እንዳይከተው የአካባቢው ነዋሪዎች ስጋታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ በሌላ ዜና ደግሞ መጋቢት27ቀን 2008 ዓም የሚከበረውን የመድሐኒዓለም ክብረበአል ለማክበር ከተለያዩ ቦታዎች ወደ ዋልድባ አብረንታንት ገዳም የሄዱ ምዕመናንን ታጣቂዎች አርማደጋ ላይ በማስቆም ከ200 በላይ የሚሆኑትን ንብረታቸውን ሙሉ በሙሉ እንደዘረፉዋቸው ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ የገዳሙ አባቶች ለኢሳት ተናግረዋል፡፡ ዘራፊዎቹ 4 ሲሆኑ፣ ሁለቱ ይፈትሻሉ ሁለቱ ደግሞ ህዝቡን ያስቆማሉ ያሉት አባቶች፣ ክላሽ፣ ጩቤና ገጀራ መያዛቸውንም አክለዋል፡፡

በአምቦ ወህኒ ቤት አንድ ወጣት በደረሰበት አሰቃቂ በድብደባ ተገደለ

አምቦ ወህኒ ቤት ውስጥ የታሰረ አንድ ወጣት በድብደባ መገደሉን ወላጅ እናቱ ለኢሳት ገለጹ። ላለፉት 10 አመታት በወህኒ ቤት ውስጥ የቆየው ወጣት ጌጡ በቀለ ቶሎሳ፣ ህይወቱ ያለፈው ከአምቦ ወህኒ ቤት ቃጠሎ ጋር በተያያዘ እጅ አለበት በሚል በደረሰበት ድብደባ መሆኑም ተመልክቷል። በፖለቲካ ሳቢያ ከ10 አመት በፊት ወህኒ ቤት መግባቱ የተገለጸው ወጣት ጌቱ በቀለ፣ እዚያው እያለ በመጣበት ተጨማሪ ክስ ወህኒ ቤት ውስጥ እንዲቆይ መደረጉን ከወላጅ እናቱ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል። የመጣበትም ተጨማሪ ክስ በአካባቢው ከተገደለ የኦህዴድ ካድሬ ጋር በተያያዘ ሲሆን፣ ገዳዩ አንተነህ በሚል ተወንጅሎ መቆየቱንም መረዳት ተችሏል። ወላጅ እናቱ በቅርቡ ወህኒ ቤት ሄደው ሲጎበኙ ጤነኛ የነበረው ጌቱ በቀለ ቶሎሳ በሳምንት ጊዜ ውስጥ ህይወቱ ማለፉን አስረድተዋል። ሆስፒታል መግባቱን ገልጾ በላከላቸው መልዕክት ሊጎበኙት ሲሄዱ አስከሬኑ መላኩ እንደተነገራቸው አስረድተዋል። አስከሬኑን ለማግኘት የደረሰባቸውን መጉላላትም ያስታወሱት የሟች ወጣት ጌቱ በቀለ ቶሎሳ እናት፣ አስከሬኑ ሲደርሳቸው ከፍተኛ ድብደባ ያደረሱበት መሆኑን ገልጸዋል። ሟች ወጣት በአካሉ ላይ በደረሰበት ድብደባ ከፊል ሰውነቱ በፋሻ መጠቅለሉንም ለኢሳት አስረድተዋል።

የቤት ለቤት ፍተሻ የመርካቶ ነጋዴዎችን አበሳጭቶአል

የገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ያለፍርድ ቤት ትእዛዝ በፖሊስ ሀይል እየታገዘ መደብሮቻችንን መፈተሽ መጀመሩ ህገወጥ እርምጃ ነው በሚል የመርካቶ ነጋዴዎችተቃውመዋል። አንዳንድ ነጋዴዎች ለአዲስ አበባው ሪፖርተራችን እንደነገሩት ፖሊሶች በድንገት ሱቆቻችንን በመውረር ፍተሻ እናደርጋለን በሚል ለእያንዳንዱ እቃ በህጋዊ መንገድ የገባበትን ማስረጃ ካላቀረባችሁ ብለው እንደሚያዋክቡ፣ አንዳንዶች ማስረጃዎችን እስከሚያሰባስቡ እድል እንኩዋን ሳይሰጡዋቸው እቃዎቻቸውን ኮንትሮባንድ ናቸው በሚል ጭነው እየወሰዱ መሆኑ አሳዛኝ ነው ሲሉ በምሬት ገልጸዋል። ነጋዴዎቹ አያይዘውም በተለይ ሞባይሎች፣ ፍሪጆች፣ ቴሌቪዥኖችና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች መንግስት በላካቸው ሀይሎች እየተዘረፉ መሆኑን ተናግረዋል። ባለስልጣኑ በበኩሉ ኮንትሮባድን ለመቆጣጠር በመርካቶ አካባቢ በተመረጡ 7 ሱቆች ላይ ሰሞኑን ድንገተኛ ፍተሻ በማካሄድ ግምታቸው 1 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሆነ የኤሌክትሮኒክስ የኮንትሮባንድ እቃዎች ይዣለሁ ብሎአል። ባለፉት ወራት በተመሳሳይ ሁኔታ በ29 ሱቆች ላይ እርምጃ መውሰዱንና በድርጊቱ የተጠረጠሩ ነጋዴዎችን እንደሚከስ አስታውቆአል። በዚህ ምክንያት በመርካቶ በተለይ አንዋር መስጊድ አካባቢ በርካታ ሱቆች አገልግሎት እየሰጡ አለመሆኑን ለመገንዘብ ተችሎአል።

በአበረታች መድሃኒት ምክንያት የኢትዮጵያ አትሌቶችና አትሌቲክስ ማኅበር ቅጣት ይጠብቃቸዋል

በኢትዮጵያ አትሌቲክስ ታሪክ ውስጥ ተደርጎ የማያውቅ ድርጊቶች በቅርቡ ከዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ማኅበርና ከመገናኛ ብዙሃን በኩል መደመጥ ተጀምርዋል። ውጤታማው የኢትዮጵያ የመሃከለኛና የረዥም ሩጫ ተወዳዳሪዎች አበረታች መድሃኒት መጠቀማቸውን የፀረ አደንዛዥ እጽ ተቆጣጣሪ ድርጅት በምህጻረ ቃሉ ዋዳ /WADA/ አስታውቋል። ዓለምአቀፉ አትሌቲክ ማኅበር የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ማኅበር የሯጮችን የደም ምርመራ ናሙና ውጤት ካላቀረበ በኢትዮጵያ ላይ ቅጣት እንደሚጥል ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ማኅበር የሕክምና ኃላፊ የሆኑት ዶክተር አያሌው ጥላሁን እንዳሉት ''ከ150 አስከ 200 በሚሆኑ ሯጮች ላይ በቅርብ ሳምንታት ውስጥ ምርመራ እንደሚጀምር ገልጸዋል። ዶክተር አያሌው አክለውም ''እኛ ምርመራውን ካላደረግን በቅርቡ ከማንኛውም ውድድሮች የሚያግድ ቅጣት እንደሚጣልብን ዓለምአቀፉ አትሌቲክስ ማኅበር አሳውቆናል'' በማለት የሁኔታውን አሳሳቢነት ተናግረዋል። የዓለም አቀፉ አትሌቲክስ ማኅበር ፕሬዝዳንት ሰር ሰባስቲያን ኮባሳለፍነው ወር ላይ እንዳሉት ኢትዮጵያ ከዋነኞቹ ተጠርጣሪዎቹ አምስቱ አገራት ሩሲያ፣ ኬንያ ፣ ሞሮኮ፣ ቤላሩስና ዩክሬን ተርታ መመደቧን አሳውቀዋል። ኢትዮጵያና ኬንያ እያንዳንዳቸው ሶስት ሯጮች ላይ እገዳ መጣላቸውን አስታውቀዋል። ዘጠኝ የኢትዮጵያ ሯጮች አበረታች መድሃኒት ሳይጠቀሙ እንዳልቀሩ ጥርጣሬ መኖሩንና ማጣራቱንም እንደሚቀጥል ማኅበሩ አስታውቋል። የአበረታች መድሃኒት ቁጥጥሯ ደካማ የተባለችው ሩሲያ ከማንኛውም ውድድሮች የታገደች ሲሆን ኬኒያና ኢትዮጵያም አስቀድመው ካላሳወቁ እገዳውን ሊጥል እንደሚችል ዓለምአቀፉ አትሌቲክ ማኅበር ማስጠንቀቂያ መስጠቱን አሾሸትድ ፕሬስ ዘግቧል።

Wednesday, 6 April 2016

ኢትዮ-ቴሌኮም ያልተቀረጡ ስልኮችን በአገልግሎት ላይ እንዳይውሉ የሚያደርግ ቁጥጥርን ተግባራዊ ሊያደርግ ነው

በኢትዮጵያ የስልክ አገልግሎትን በብቸኝነት እየሰጠ የሚገኘው ኢትዮ-ቴለኮም በተለያዩ መንገዶች ወደ ሃገሪቱ የገቡና ያልተቀረጡ ስልኮችን በአገልግሎት ላይ እንዳይውሉ የሚያደርግ ቁጥጥርን ተግባራዊ ሊያደርግ መሆኑን አስታወቀ። ኢኪዩፕመንት አይደንቲቲ ሬጂስተር የተሰኘ ቴክኖሎጂን አገልግሎት ላይ ለማዋል በዝግጅት ላይ የሚገኘው ድርጅቱ በሃገሪቱ ያሉ ሁሉ የእጅ ስልኮች ምዝገባ እንደሚያደርጉም ገልጿል። በምዝገባው ያልተካተቱና በስጦታና በተለያዩ መንገዶች ወደ ሃገር ውስጥ የገቡ ስልጎችም ተገቢው ምርመራ ካልተካሄደባቸው በስተቀር በአገልግሎት ላይ እንዳይዉሉ የሚደረግ መሆኑን የኢትዮ-ቴሌኮም ሃላፊዎች ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ይፋ አድርገዋል። በተለያዩ መንገዶች ወደሃገሪቱ የገቡና በአገልግሎት ላይ የሚገኙ ስልኮችም በምን መልኩ ህጋዊ መደረግ እንዳለባቸው ከቀናት በኋላ ጉዳዩ የሚመከለታቸው አካላት ምክክርን ያካሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የብሪታኒያ ፓርላማ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይን በልዩ ሁኔታ ለመከታተል ወሰነ

የብሪታኒያ ፓርላማ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ በእስር ላይ የሚገኙትን የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይን በልዩ ሁኔታ ለመከታተል ወሰነ። የሃገሪቱ መንግስት የዜጋውን መብት ለማስጠበቅ የተቻለውን ሁሉ አላደረገም ሲሉ የቀረቡ አቤቱታዎችንና ተቃውሞዎችን ዋቢ በማድረግ ኮሚቴው የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ጉዳይ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ለመከታተል እንደወሰነ የብሪታኒያ መገናኛ ብዙሃን ረቡዕ ዘግበዋል። የብሪታኒያ መንግስት ለሰብዓዊ መብት መከበር በቂ ትኩረት አለመስጠቱን የተቸው የፓርላማው የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ሃገሪቱ በሰብዓዊ መብት አያያዝ የጎደፉ ስም ያላቸውን ሃገራት ለማውገዝ እንኳን አለመድፈሩ ስጋትን እንዳሳደረም አመልክቷል። የአውሮፓ ፓርላማና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ከእስር እንዲለቀቁ ጥያቄን ቢያቀርቡም፣ የብሪታኒያ መንግስት ተመሳሳይ ጥያቄን አለማቅረቡም በኮሚቴው ትችት ቀርቦበታል። በእነዚህና በሌሎች ጉዳዮች ዙሪያ በሃገሪቱ መንግስት ላይ ተቃውሞን ያቀረበው ኮሚቴው የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይን ጨምሮ ሌሎች አበይት ጉዳዮችን በልዩ ሁኔታ ለመከታተል እንደወሰነ ይፋ አድርጓል። በቅርቡ በኢትዮጵያ ጉብኝት ያደርጋሉ ተብለው የሚጠበቁት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዴቪድ ካሜሩን የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይን ልዩ ትኩረት ሰጥተው እንዲያነሱም የተለያዩ አካላት ግፊት እያደረጉ እንደሆነም ታውቋል። ከአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ በተጨማሪ የብሪታኒያ ፓርላማ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ በግብፅ በእስር ላይ የሚገኝን የአንድ የአየርላንድ ታዳጊ ወጣት ጉዳይንም በልዩ ሁኔታ እንደሚከታተለው ገልጿል። ታዳጊ ወጣቱ ከሶስት አመት በፊት በካይሮ ከተማ በተካሄደ አንድ የተቃዋሚ ሰልፍ ላይ ተሳታፊ ሆኗል ተብሎ በቁጥጥር ስር ውሎ የሚገኝ ሲሆን የሞት ቅጣት ይተላለፍበታል ተብሎ ተሰግቷል። የብሪታኒያ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋም የሆነውና የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይን የሚከታተለው ሪፕሪቭ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ማያ ፎያ ፓርላማው የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች በልዩ ሁኔታ ለመከታተል መወሰኑ ተገቢና ወቅታዊ መሆኑን አስታውቀዋል። የብሪታኒያ አጋር የሚባሉት ኢትዮጵያ ግብፅ ተደጋጋሚ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እየፈጸሙ እንደሆነም ሃላፊዋ አክለው ገልጸዋል።

Tuesday, 23 February 2016

በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ለመቆጣጠር ህወሃት/ኢህአዴግ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ለመቆጣጠር ህወሃት/ኢህአዴግ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ
ኢሳት (የካቲት 15 ፥ 2008)
በኦሮሚያ ክልል ለሶስተኛ ወር ቀጥሎ ያለውን ተቃውሞ ለመቆጣጠር መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ማክሰኞ አስታወቀ። 
በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫን የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ በክልሉ በበርካታ አካባቢዎች እየተካሄደ ካለው ተቃውሞ ጀርባ የጥፋት ሃይሎች ይገኛሉ ሲሉ ገልጸዋል። 
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተደራጁ የጥፋት ሃይሎች ያሏቸውን አካላት በስም ባይጠቅሱም መንግስትን የማፈራረስና የመቀየር ተልዕኮ አላቸው ሲሉ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። 
ድርጊቱንም ለመቆጣጠር መንግስት የማያዳግም እርምጃን እንደሚወስድ ገልጸው በምዕራብ አርሲና በሃረር አካባቢዎች ተቃውሞ መቀጠሉን አመልክተዋል።
የአሜሪካ መንግስትና የአውሮፓ ህብረት የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች እየወሰዱ ያለውን የሃይል እርምጃ በማውገዝ የኢትዮጵያ መንግስት ከድርጊቱ እንዲቆጠብና ለተቃውሞ ሰላማዊ ምላሽን እንዲሰጥ ማሳሰባቸው የታወሳል።
በክልሉ እየተካሄደ ያለው ተቃውሞ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ያለፉ የመብት ጥያቄን ያካተተ እንደሆነ የሚገልጹት እነዚሁ አካላት በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመ ግድያን ማጣራት እንዲካሄድበት ጠይቀዋል።
በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ሰኞ መግለጫን ያወጣው ሂውማን ራይትስ ዎች በበኩሉ ሶስተኛ ወሩን በያዘው ተቃውሞ ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸውንና እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠሉን አመልክቷል።
የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በኦሮሚያ ክልል ቀጥሎ ያለው ተቃውሞ መፍትሄን እንዲያገኝ በመጠየቅ ላይ ቢሆኑም መንግስት የጥፋት ሃይሎች እጅ አለበት በማለት የሚወስደውን የሃይል እርምጃ እንደሚቀጥል ማክሰኞ ገልጿል።

Sunday, 21 February 2016

የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አዛዦች በአዲስ አበባ ስብሰባ አካሄዱ፡፡ ስብሰባው ያለምንም ውጤት በግጭት ተቋጭቷል


የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አዛዦች በአዲስ አበባ ከየካቲት 9 እስከ 12 2008 ዓ.ም የተሰበሰቡ ሲሆን የመልካም አስተዳደር ችግር፣ የፀጥታ ሁኔታ እና የአባላት መክዳት እያነሱ ከተወያዩባቸው አጀንዳዎች መካከል ዋነኞቹ ናቸው፡፡ በስብሰባው ላይ የአማራና የኦሮሞ ተወላጅ አዛዦች "እኛ ከእናንተ የተሻለ የትምህርት ደረጃና ልምድ እያለን ሁሉንም ቦታ ጠቅልላችሁ ይዛችሁት ተገቢው ቦታ አልተሰጠንም..." በማለት ህወሓቶችን ልካቸውን ነግረዋቸዋል፡፡
ህወሓቶች በፌደራል ፖሊስ ተቋም ውስጥ ባሰፈኑት ዘረኝነት ምክንያት ሰራዊቱ በመፍረስ ላይ እንደሚገኝ ስብሰባው ላይ በተደጋጋሚ ...ተወስቷል፡፡ በውይይቱ ላይ ተቃውሟቸውን ያሰሙ የኦሮሞና አማራ ተወላጅ አመራሮች ከህወሓቶች "የእናስራችኋል" ማስፈራሪያ ደርሷቸዋል፡፡
በመጨረሻም ስብሰባው ወደ ለየለት ንትርክና አምባጓሮ በማምራቱ አብዛኞቹ አዛዦች እንዲበተኑ ተደርገው ውይይቱ በጥቂት ዋና፣ ዋና አመራሮች ለተጨማሪ ጊዜ ተካሂዷል፡፡ የፌደራል ፖሊስ አደረጃጀት ሊፈርስ እንደሚችልም ጭምር ጭምጭምታ ተሰምቷል፡፡
በተያያዘ ዜና የሚከዱ የፌደራል ፖሊስ አባላት ቁጥር አሁንም ከቀን ወደ ቀን እየናረ መምጣቱ እየተነገረ ነው፡፡ በጎንደር ብቻ ቢያንስ በቀን 3 የፌደራል ፖሊስ አባላት እንደሚከዱ የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ ዜና ምንጮች ገልፀዋል፡፡
 #የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ#

የ24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በገፍ እየገዱ መሆናቸው ታወቀ

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
የ24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በገፍ እየገዱ መሆናቸው ታወቀ፡፡
በሰሜን ምዕራብ የኢትዮጵያ ክፍል በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለረጅም ዓመታት የዘለቀ የሽምቅ ውጊያ ጥቃት ሲደርስበት፣ እስከ ሬጅመንት ድረስ እየተደመሰሰ ሲፈርስና እንደገና በሰው ኃይልና በጦር መሳሪያ በተደጋጋሚ ሲገነባ የኖረው 24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በውጊያ በእጅጉ ተሰላችተውና በስርዓቱ ተስፋ ቆርጠው በከፍተኛ ሁኔታ በመክዳት ላይ ናቸው፡፡
በተለይም ደግሞ የሽምቅ ውጊያ ጥቃቶች የመጀመሪያ ገፈት ቀማሽ የሆኑ በሁመራና አካባቢው ሰፍረው የቆዩ ሬጅመንቶች ውልቃቸውን በመቅረታቸው ከአዘዞ እና ጭልጋ ሌሎች ሬጅመንቶችን አንስቶ የመተካት እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡
የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ የነፃነት ድርጅቶች ክንድ እየፈረጠመ መምጣት እና ዕለት ከዕለት በሚያደርጓቸው የሽምቅ ውጊያ ጥቃቶች የሚያሳርፉት ዱላ እየበረታ መሄድ በዋነኝነት አርበኝነት በሚፋፋምበት አካባቢ የሚገኘውን 24ኛ ክፍለ ጦር አፍረክርኮታል፡፡

Friday, 19 February 2016

እነ በቀለ ገርባና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ለመጋቢት 9 ተቀጠሩ

እነ በቀለ ገርባና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ለመጋቢት 9 ተቀጠሩ
*ጋዜጠኛ ጌታቸው ጨለማ ቤት ታስሯል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብር ተጠርጥረው በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኙት የኦፌኮ አመራሮች እነ በቀለ ገርባ እና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው የ28 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ዛሬ የካቲት 11/2008 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት የቀረቡት የኦፌኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ በቀለ ገርባ እና በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ ሌሎች የፓርቲው አባላት፣ እንዲሁም ታህሳስ 15/2008 ዓ.ም ለእስር የተዳረገው የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው እና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ ዳንኤል ተስፋየ ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም በሚል የጠየቀባቸው የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተፈቅዶለታል፡፡...
የጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን ከችሎቱ በኋላ እንደገለጹት ፖሊስ ‹‹ግብረ አበር መያዝ ይቀረኛል፣ ምስክር አላደራጀሁም…›› የሚል ካለፈው ጋር ተመሳሳይ ምክንያት በመስጠት ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል፡፡ ደንበኛቸው ከታሰረ ጀምሮ አንድም ቀን አግኝተው ለማነጋገር እንዳልተፈቀደላቸው ለችሎት የገለጹት ጠበቃ አምሃ፣ ጌታቸው ጠበቃውን ሳያነጋግር ቃሉን ለፖሊስ ለመስጠት ፍቃደኛ እንዳልሆነ ፍርድ ቤቱ እንዲገነዘብላቸው በድጋሜ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡
ጋዜጠኛ ጌታቸው በበኩሉ ያለፉትን 28 የምርመራ ቀናት የተጠየቀው ነገር እንደሌለ፣ ነገር ግን በጨለማ ቤት እንዳሰሩት ለችሎት ገልጹዋል፡፡
በተመሳሳይ የምርመራ መዝገብ የሚገኙት አቶ ዳንኤል ተስፋየ እና አቶ ሸዋታጠቅ ኃ/መስቀል በበኩላቸው ቤተሰቦቻቸው እንዲጠይቋቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡
በተመሳሳይ ችሎት የቀረቡት እነ በቀለ ገርባም እንዲሁ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸው 28 ቀናት ተፈቅዶለታል፡፡ የዛሬውን የችሎት ውሎ ለመከታተል የተጠርጣሪዎች ቤተሰቦችና ወዳጆቻቸው ፍርድ ቤት ግቢ ቢገኙም ችሎቱ ዝግ በመደረጉ አንድም ሰው መከታተል እንዳልቻለ ታውቋል፡፡


Sunday, 14 February 2016

በጎንደር ከተማ የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ አባላት በገፍ እየከዱ ነው

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
‪#‎በጎንደር‬ ከተማ የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ አባላት በገፍ እየከዱ ነው፡፡
በጎንደር ከተማና አካባቢው የጦር ካምፕ መስርተውም ሆነ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሱ አገዛዙን ሲያገለግሉ የቆዩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በከፍተኛ ሁኔታ ከነትጥቃቸው በመሰወር ላይ ናቸው፡፡ ባለፈው ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ30 በላይ ፌደራል ፖሊሶች ከነትጥቃቸው ስርዓቱን በመቃወም ከየካምፓቸውና በውሎ ጠፍተዋል፡፡
የህወሓት አገዛዝ ይህን የፌደራል ፖሊስ አባላት መክዳት ለማስቆም ተደርጎ የማይታወቀውን ጥቅማጥቅምና የማዕረግ እድገት ለመስጠት ቢወስንም ሰራዊቱ እንደበፊቱ በቀላሉ ተሸውዶ ሰጥ ለጥ ብሎ ወደ ሎሌነት ተግባሩ ሊመለስ አልቻለም፡፡ እንዴውም በተቃራኒው የሚጠፉ የፌ...ደራል ፖሊስ አባላት ቁጥር ከቀደመው ጊዜ ጋር ሲነፃፀር አየናረ መጥቷል፡፡
በመሆኑም ለዛሬ ሰፊ ስብሰባ ሊደረግ ፕሮግራም ተይዟል፡፡


Saturday, 13 February 2016

በጎንደር ከተማ ጎሃ ሆቴል ውስጥ ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ በተካሄደው ስብሰባ

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የአማራ ክልል ሹሞች በጎንደር ጎሃ ሄቴል ለሦስት ተከታታይ ቀናት ያደረጉት ድብቅ ስብሰባ ያለምንም ውጤት በፀብ ብቻ ተቋጨ፡፡ በህወሓቶችና በብአዴኖች መካከል የተካረረ ፍጥጫና ንትርክ ተከስቶ የነበረ መሆኑም ተደርሶበታል፡፡
===================================================
በጎንደር ከተማ ጎሃ ሆቴል ውስጥ ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የተገኙት የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናት አባይ ፀሐዬ፣ ስብሃት ነጋ፣ ደብረ ፂዮን ገ/ሚካኤል፣ አባይ ወልዱ እና የትግራይ ክልል አስተዳደርና ፀጥታ ሹም ናቸው፡፡
ገዱ አንዳርጋቸው፣ አለምነው መኮንን እና መኳንንት /የአማራ ክልል ፀጥታ ሹም/ ደግሞ ከብአዴን ወገን የተገኙ የአማራ ክልል ሹማምንቶች ነበሩ፡፡
የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የህወሓት ዲቃላ የሆነው ብአዴን ባለስልጣናት በጎንደር ጎሃ ሆቴል ተሰብስበው የተነታረኩባቸው አጀንዳዎች ሁለት ሲሆኑ የወልቃይትን የአማራ ማንነት ጥያቄ እና ብረት ያነሱ የነፃነት ድርጅቶችን /በተለይም አርበኞች ግንቦት 7ን/ በሚመለከት ነው፡፡
የትጥቅ ትግል እያደረጉ የሚገኙ የነፃነት ድርጅቶችን በሚመለከት ህወሓቶች "ሰተት ብለው ከበረሃ ወደ ህዝቡ እንዲገቡ እያደረጋችኋቸው ነው..." በማለት ብአዴኖችን ወቅሰዋቸዋል፡፡
ከወልቃይት ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ደግሞ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪና የህወሓት ሊቀ መንበር የሆነው አባይ ወልዱ እንዲህ ብሏል፡፡
"ወልቃይት የትግራይ ነው! የአማራነት ጥያቄው በዚህ የማያቆምና ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን...!"
ቀጥሎም አባይ ወልዱ የአማራ ክልልን አስተዳዳሪ ገዱ አንዳርጋቸውን
"አንተ የአማራን ህዝብ የጦር መሳሪያ ያስታጠከው ሆነ ብለህ በትግራይ ላይ ጦርነት ለማወጅ ነው..." በማለት ተናግሮታል፡፡
ገዱ አንዳርጋቸውም በበኩሉ
"እኔ ህዝቡ በሀብቱ ገዝቶ ከጥንት ጀምሮ ታጥቆት የቆየውን ጦር መሳሪያ ህጋዊ ፈቃድ በመስጠት አፀናሁለት እንጂ ልክ እንዳንተ ከመንግስት ግምጃ ቤት አውጥቼ በገፍ አላስታጠቁትም፡፡ በትግራይ ህዝብ ላይ ጦርነት አወጅክ ላልከኝም የትግራይን ህዝብ ሰብስበህ በወልቃይት ህዝብ ላይ እርምጃ እንወስዳለን ብለህ በይፋ ጦርነት ያወጅከው አንተ ነህ፡፡" በማለት ለአባይ ወልዱ መልስ ሰጥቶታል፡፡
የጦር መሳሪያን በሚመለከት ደብረ ፂዮን ገ/ሚካኤል ገዱ አንዳርጋቸው የአማራን ህዝብ እንዳስታጠቀ ወቀሳ ሰንዝሯል፡፡ ደብረ ፂዮን ስለ ወልቃይት ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ የሚከተለውን በማለት ቁልጭ ያለ አቋሙን አስቀምጧል፡፡
"የወልቃይት ጉዳይ ክልል አንድን እንጂ ማንንም አይመለከተውም፤ ውሳኔውም ሊሆን የሚችለው የክልል አንድ ብቻና ብቻ ነው፡፡"
ለዚህ የደብረ ፂዮን ንግግር ገዱ አንዳርጋቸው ሲመልስ
"እኛ ሄደን ኑ አንላቸውም፤ ከመጡ ግን የማንቀበልበት ምንም ምክንያት የለም፤ ደግሞም ውሳኔ ማስቀመጥ ያለበት ራሱ የወልቃይት ህዝብ ነው፡፡"
በመሆኑም በሁለቱ ክልሎች /በትግራይና አማራ/ አስተዳዳሪዎች ማለትም በአባይ ወልዱና ገዱ አንዳርጋቸው መካከል ስብሰባው ውስጥ የተካረረ ፍጥጫ ተከስቶ ነበር፡፡
ህወሓቶች ለገዱ አንዳርጋቸው ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጥተውታል፡፡
በአጠቃላይ በጎንደር ጎሃ ሆቴል ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ የተካሄደው የህወሓቶችና የብአዴኖች ውይይት ያለምንም መግባባት በፀብ ብቻ ተጠናቋል፡፡

Thursday, 11 February 2016

ኦሮሚያ የመላው ኢትዮጵያዊ መላው ኢትዮጵያም የሁሉም ኦሮሞ ናት!

ኦሮሚያ የመላው ኢትዮጵያዊ መላው ኢትዮጵያም የሁሉም ኦሮሞ ናት!
ከጃዋር ሃሳብ የማልስማማበት እና የምስማማበትን ስለመለየት፤
የኛ ሀገር ፖለቲካ የቡዳ ፖለቲካ ነው እንዳሉት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አሁንም ድጋሚ ፖለቲካችንን ቡዳ ሊበላው ነው መሰል ጣት መቀሳሰር እና እነ እንትና እነ እንትና መባባል ልንጀምር ይመስላል… ምናባቱ እንግዲህ ካልደፈረሰ አይጠራም…
ጃዋር ሰሞኑን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዋሽንግተን ዲሲ ካደረጉት ንግግር በኋላ በአራት ጉድዮች ላይ አስተያየት ሰጥቷል። ካነሳቸው ሃሳቦች ውስጥ በተወሰነ ደረጃ የምስማማባቸው ሃሳቦች ቢኖሩኝም በርካታ የማልስማማባቸው ሃሳቦችም አሉ። ከሁሉ ከሁሉ ግን በትልቁ የማልስማማበት፤ ኦሮሞ በሙሉ ተመሳሳይ ነው ብሎ ሁሉንም ኦሮሞዎች በአንድ ቅርጫት ውስጥ ለማስቀመጥ የሚሞክረው ነገር ሁልጊዜም በጣም የሚያበሳጨኝ ነው። (እነደሱ አባባል እርሱ በሚለው የማይስማማ ኦሮሞ ኦሮሞ አይደለም (ሲያናድድ!))
እኛ ኦሮሞዎች ሰዎች ነን። ምንም እንኳ የሰው ልጆች በሙሉ በፍጥረታቸው አንድ ናቸው ቢባልም፤ በአስተሳሰብ እና በአመለካከት ግን አንድ አይነት መሆን አይችሉም። ሁሉም ሰው የየራሱ አመለካከት እንዳለው ሁሉ፤ ኦሮሞዎችም የየራሳችን አመለካከት አለን። እኛ በፋብሪካ የተመረትን ሮቦቶች አይደለንም። የተለያየ አመለካከት የተለያየ አስተሳሰብ፣ የተለያየ የምፍትሄ አቅጣጫ፣ የተለያየ ምኞት እና ፍላጎት ያለን ሰዎች ነን። ይሄ ሰው በመሆናችን የተሰጠንም ጸጋ ነው። ጃዋር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ ‘’ከለዘብተኛ ኦሮሞዎች ጋር አብረን እየሰራን ነው’’ ማለቱን ተከትሎ በኦሮሞ ውስጥ ለዘብተኛ አክራሪ የለም ብሎ ይሞግተናል። ሞልቶ! በሁሉም ማህበረሰብ ውስጥ በአንድ ጉዳይ ላይ አክራሪ እና ለዘብተኛ እንዳለው ሁሉ በኦሮሞ ማህበረሰብ ውስጥም ይሄ አለ። ወደፊትም ይኖራል።
ለምሳሌ ያክልም፤ ራሱ ከጃዋር እና የመሳሰሉት ኦሮሚያ የኦሮሞ ናት ሲሉን እየሰማን ነው። በነገራችን ላይ የ ‘የ’ እና የ ’ለ’ ነገር በትርጉሙ ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም። ኦሮሚያ ለኦሮሞ ናት ተባለም ኦሮሚያ የኦሮሞ ናት ተባለም ምንም የፍቺ ልዩነት የላቸውም። (ወዳጃችን ጃዋር ኦሮሚያ ለኦሮሞ ናት አላልኩም ኦሮሚያ የኦሮሞ ናት ነው ያልኩት ሲል አይቼ ባውጠነጥን ባውጠነጥን ምንም ልዩነት አላየሁበትም።) የሆነው ሆኖ ጃዋር እንደሚያስበው ይሄ አስተሳሰብ የሁሉም ኦሮሞዎች አስተሳሰብ ነው። በኦሮሚያ የተነሳው ተቃውሞም ዋና ሃሳብ ይሄ ነው ይለናል።
እኛ ጃዋር ኦሮሞ አይደለም ብለን አንከራከርም። ነገር ግን እርሱ ብቻ ሳይሆን እኛም ኦሮሞዎች ነን። እንደኛ አስተሳሰብ ኦሮሚያ የመላው ኢትዮጵያዊ መላው ኢትዮጵያም የኦሮሞ ናት። እንኳንስ ኦሮሚያ እና ብሪታኒያ እና አሜሪካንን የመሳሰሉት ሀገሮች እንኳን የብርትሾች እና የአሜሪካኖች አይደሉም፤ የሁላችንም ናቸው እንጂ! (ምንም እንኳ እንደ ዶናልድ ትራምፕ አይነት ቀውሶች ይሄ አሳብ ቅዠት ቢመስላቸውም አሁን አለም ባለችበት ደረጃ ግን ማንም ሰው የሀገሪቱን ህግ እና ደንብ አክብሮ እስከኖረ ድረስ ሁሉም ሀገር የሁሉም ነው። በዛ መሰረት ነው ጃዋርም ሆነ እኔ በአሜሪካ እና እንግሊዝ የምንኖረው!)
በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ተቃውሞ ዋና ማጠንጠኛ ኦሮሞ ዘመዶቻችን አንድም በገዛ ወገኖቻቸው፤ (በኦህዴድ አባላት) አንድም ከፌደራል በሚሄዱት እነ አባይ ጸሃዬ የሚደርስባቸው ስር የሰደደ በደል ሞልቶ ስለፈሰሰ ነው፤ እንጂ ኦሮሚያ ለኦሮሞ ትሁን በሚል አይደለም። እንደዚ የሚሉ ቢኖሩም እንኳ በኔ አስተሳሰብ ስህተት ውስጥ እየገቡ ነው። ማንም ሰው በአግባቡ እና በደንቡ መሰረት እስከተንቀሳቀሰ ድረስ (በእግር ኳስ ቋንቋ ፌር ፕሌይ እስከተጫወተ) ሁሉም ሃገር የርሱ ነው። ኦሮሚያን ጨምሮ። ብቻ ገበሬዎችን ያለአግባብ አያፈናቅል። ብቻ ገበሬውን በገዛ መሬቱ ላይ ከአምራችነት ወደ ዘበኛነት አይቀይር እንጂ!
አሁን ኢህአዴግ እየፈጸመ ያለው ዘረፋ በኦሮሚያ ላይ ነውር ነው! በትግራይም ላይ ሲፈጸም ብልግና ነው! በአማራ ክልልም ሲደረግ ጸያፍ ነው።
ይልቅስ ጃዋር በብሄር ስለመደራጀት ያነሳው ነገር ላይ እስማማለሁ። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይሄ የኔ አመለካከት ነው ብለው በነገሩን መሰረት የብሄር ወይም ዘውጌ ፖለቲካዊ ስብስብ አይመስጣቸውም ብቻ ሳይሆን አፍራሽ ነው ሲሉም ኮንነውታል። በርግጥ ‘’እባብን ያየ በልጥ ይደነግጣል’’ እንዲሉ አሁን አሁን እየሆነ እንዳለው ነገር የብሄር አደረጃጀቶች የሚያስፈራ ነገር አላቸው። ቢሆንም ግን አፍራሽ ናቸው ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ ከባድ ነው። ሰዎች በመሰላቸው መልኩ የመደራቸት እና የመታገል መብታቸው በጽኑ ሊከበር ይገባል። በሰለጠኑት ሃገራት በብሄር የተደራጁ ፓርቲዎች ለዴሞክራሲ ግንባታ አፍራሽ ሚና ሲጫወቱ አላየንም። እንደ ምሳሌም ስኮቲሽ ናሽናል ፓርቲ በ ዩናይትድ ኪንግደም ፖለቲካ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ማየት ይቻላል። እኛም ሃገር ቢሆን ፖለቲካችን አፍራሽ ሚና የሚኖረው ከአያያዛችን እንጂ ከአደረጃጀታችን አይመስለኝም። (እንደውም ከቤተሰብ ጉባኤ አንስቶ ብብሄር መደራጀት ተፈጥሯዊ ነው ብዬ አስባለሁ.... አፍራሽ የሚሆነው ክኔ ብሄር በላይ ላሳር ማለት ሲጀመር ነው! እሱን የሚገራ ሀገር አቀፍ ህግ መኖር ይኖርበታል!)
በኢሳት ቴሌቪዥን የኦሮምኛ ቋንቋ ዝግጅቶች መጀመራቸውን አስመልክቶ የኦሮሞን ህዝብ ትግል ለማዳከም ነው የሚለን ጃዋር ከላይ እንዳነሳሁት በኢሳት ቴሌቪዥን ላይ በአዘጋጅነት የሚሰሩትን ኦሮሞዎች ስለ ኦሮሞ ጉዳይ የማያስቡ ራሱን ደግሞ ከማንም በላይ ለኦሮሞ አሳቢ የማድረግ አዝማሚያ ነው ያየሁበት... ይሄኔ ይቺ ሰውዬ ቀስ ብላ እኔንም ለኦሮሞ አታስብም ትለኝ ይሆናል እኮ ብዬ ስቄ ትቼዋለሁ!
እያልኩ ልጻፍ ልተወው… በማለት እያሰብኩ ነው….
(ጋዜጠኛ አበበ ቶላ ፈይሳ አቤ ቶኪቻው)

Friday, 5 February 2016

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የምስክርነት ቃሉን ሰጠ

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የምስክርነት ቃሉን ሰጠ
*‹‹የህሊና እስረኛ ነኝ›› እስክንድር ነጋ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ 18 አመት እስር ተፈርዶበት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የመከላከያ ምስክርነት ቃሉን ሰጥቷል፡፡ 
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ ለሆነው አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ መከላከያ ምስክር ሆኖ ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ከእስር ቤት የቀረበው ጋዜጠኛ እስክንድር ዛሬ ጥር 27/2008 ዓ.ም ምስክርነቱን ሊያሰማ ችሏል፡፡ 
*‹‹የህሊና እስረኛ ነኝ›› እስክንድር ነጋ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ 18 አመት እስር ተፈርዶበት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የመከላከያ ምስክርነት ቃሉን ሰጥቷል፡፡ 
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ ለሆነው አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ መከላከያ ምስክር ሆኖ ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ከእስር ቤት የቀረበው ጋዜጠኛ እስክንድር ዛሬ ጥር 27/2008 ዓ.ም ምስክርነቱን ሊያሰማ ችሏል፡፡ 
ያለጠበቃ በግሉ የሚከራከረው ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ጋዜጠኛ እስክንድር እንዲያስረዳለት የሚፈልገው ጭብጥ ጡመራ ምንድነው፣ ከወንጀል ጋርስ ግንኙነት አለው ወይ፣ እና ሰብዓዊ መብት እና ዴሞክራሲ ላይ ስልጠና ስለሚሰጡ ድርጅቶችና የስልጠናው ይዘትን በተመለከተ እንደሆነ ቢያስታውቅም በጭብጡ ላይ አቃቤ ህግ ተቃውሞውን አሰምቷል፡፡ በዚህም አቃቤ ህግ ጡመራ ምንድነው፣ ወንጀልስ ነው ወይ የሚለው በምስክር ሳይሆን በህግ ድንጋጌዎች የሚረጋገጥ እንደሆነ በመግለጽ ተቃውሟል፡፡ ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ከሰማ በኋላ ጡመራ ወንጀል ስለመሆን አለመሆኑ የተያዘውን ጭብጥ ውድቅ በማድረግ ስለ ስልጠናውና አሰልጣኝ ተቋማት የተመዘገበው ጭብጥ ላይ ምስክሩ እንዲመሰክሩ ብይን ሰጥቷል፡፡
ብይኑን ተከትሎ ምስክሩ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ችሎት ፊት የቀረበ ሲሆን በመጀመሪያ በፍርድ ቤቱ የቀረቡለትን ጥያቄዎች መልሷል፡፡ ምስክሩ ሙሉ ስሙን፣ እድሜውን፣ ስራውንና ለምን እንደመጣ፣ እንዲሁም ከተከሳሾች ጋር ስለመተዋወቁ ለቀረቡለት ጥያቄዎች መልስ ሰጥቷል፡፡ እስክንድር ‹‹ስራ›› ተብሎ ሲጠየቅ፣ ‹‹ጋዜጠኛ ነበርኩ›› ብሏል፡፡ ‹‹አሁንስ›› የሚል ጥያቄ ፍርድ ቤቱ አቅርቦለት፣ ‹‹አሁን የህሊና እስረኛ ነኝ›› ሲል መልሷል፡፡
ተከሳሹ ዘላለም ወርቃገኘሁ በዋና ጥያቄ ተከሳሹ ውጭ ሀገር ሊወስደው ነበር ተብሎ በክሱ ላይ ስለተጠቀሰው ስልጠና ምስክሩ እንዲያብራሩለት ጠይቋል፡፡ ምስክሩም ‹‹ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሀገራትንም የሚያሳትፍ ስልጠና በሰብዓዊ መብት፣ በሚዲያ ‹ኢቲክስ›፣ እና በዴሞክራሲ ላይ ይሰጣሉ፡፡ ድርጅቶቹ የተለያዩ ቢሆንም በሰብዓዊ መብት ጉዳይ ላይ መርሃቸው ተመሳሳይና ዓለም አቀፍ ነው›› በማለት መስክሯል፡፡
ድርጅቶቹን በስም መጥቀስና የሚገኙበትንም ሀገር ለፍርድ ቤቱ መግልጽ ይቻል እንደሆነ ምስክሩ ተጠይቆ ‹‹የተቋማቱ መገኛ ምዕራቡ ዓለም ነው፡፡ በዴሞክራሲ የዳበሩ ሀገራት ነው ዋና መቀመጫቸው፡፡ ሲ.ፒጄ፣ ፍሪደም ሀውስ፣ አምንስቲ ኢንተርናሽናል እና አርቲክል 19 የመሳሰሉትንም በስም መጥቀስ ይቻላል፡፡ እኔም ከነዚህ ተቋምት ውስጥ በአንዱ የተሰጠ ስልጠና አዲስ አበባ ላይ ተካፍየ ነበር፡፡ ስልጠናው ስለ ሰብዓዊ መብት፣ ስለ ሚዲያ፣ ስለ ዴሞክራሲ የሚያስተምር ነው፡፡ ስልጠናው ከሽብር ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፤ ይህ እንደማስረጃ መቅረቡ ኢትዮጵያን ትዝብት ውስጥ የሚከትና የሚያሳዝን ነው›› ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ መቼ እንደታሰረ በመስቀለኛ ጥያቄ ተጠይቆ ‹‹መስከረም 2004 የሀሰት ክስ ቀርቦብኝ፣ በግፍ ተፈርዶብኝ ታስሬ እገኛለሁ›› ሲል መልሷል፡፡ እስክንድር ነጋ ጥቁር ሱፍ በደብዛዛ ሸሚዝ ለብሶ፣ ሙሉ ጥቁር መነጸር አድርጎና ነጠላ ጫማ ተጫምቶ ችሎት ፊት ቀርቧል፡፡
አንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ምስክሩ ምስክርነቱን ማጠቃለሉን ተከትሎ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡለት የጠራቸው ሌላኛው ምስክር አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በተደጋጋሚ እንዲቀርቡለት ትዕዛዝ እንዲሰጥለት የጠየቀ ቢሆንም እስካሁን አለመቅረባቸው መንግስት ግለሰቡን ለማቅረብ ፍላጎት እንደሌለው ያሳያል ሲል ቅሬታውን አሰምቷል፡፡ ‹‹አሁን የተረዳሁት ነገር ከሳሼ የሆነው መንግስት አቶ አንዳርጋቸውን ከሚያቀርብ እኔን በነጻ መልቀቅ እንደሚቀለው ነው›› ብሏል ተከሳሹ፡፡
ተከሳሹ ከአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጋር በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች እንደተገናኜ አቃቤ ህግ መጥቀሱን በማስታወስ ምስክሩ መቅረባቸው ያለውን ተገቢነት አስረድቷል፡፡ ‹‹ምስክሩ እንዲቀርቡልኝ እፈልጋለሁ፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ፍርድ ቤቱ ከምስክሩ ጋር በተገናኘ ያለውን የክሱ ፍሬ ነገር አውጥቶ በቀሪው ላይ ብይን ይስጥልኝ›› ብሏል ተከሳሹ አቶ ዘላለም፡፡
ፍርድ ቤቱም ምስክሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲቀርቡ ትዕዛዝ በመስጠት ምስክርነታቸውን ለመስማት በሚል ለየካቲት 16/2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Thursday, 4 February 2016

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በፍርድ ቤት እየተጉላሉ መሆኑን አቤቱታ አሰማ

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በፍርድ ቤት እየተጉላሉ መሆኑን አቤቱታ አሰማ
*ተከሳሾች ችሎቱ እንዲቀየርላቸው ጠይቀዋል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14ኛ ወንጀል ችሎት እየታየ የሚገኙት እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ በፍርድ ቤት እየተጉላሉ መሆናቸውን በመግለጽ ችሎት እንዲቀየርላቸው አቤቱታ አቅርበዋል፡፡
ዛሬ ጥር 26/2008 ዓ.ም ልደታ ፍርድ ቤት የቀረቡት ተከሳሾች አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ ወ/ት እየሩሳሌም ተስፋው፣ አቶ ፍቅረማርያም አስማማው እና አቶ ደሴ ካህሳይ ጉዳያቸውን እያየ የሚገኘው 14ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳያቸውን በማጓተት እያጉላላቸው እንደሆነ በአቤቱታቸው ገልጸዋል፡፡ መዝገቡ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው ለብይን ቢሆንም ተከሳሾች 14ኛ ወንጀል ችሎት እንዲቀየርላቸው አቤቱታ በማሰማታቸው ብይኑ ሳይሰማ ቀርቷል፡፡
1ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ‹‹አቃቤ ህግ አንድ ምስክሩን ያሰማው ነሐሴ 12/2007 ዓ.ም ነው፡፡ የአንድ ምስክር ቃል በጽሁፍ ተገልብጦና ተመርምሮ ብይን ለመስራት ይህን ያህል ጊዜ መውሰድ አልነበረበትም፡፡ ለዚህ ሁሉ መጉላላት ይህ ችሎት አስተዋጽኦ አለው ብለን ስለምናምን ችሎቱ እንዲቀየርልን ለፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት ቢሮ አቤት ብለናል፡፡ ስለዚህ ብይኑ ዛሬ ሊሰማብን አይገባም›› ብሏል፡፡
3ኛ ተከሳሽ ፍቅረማርያም አስማማው በበኩሉ ‹‹ችሎቱ ለአቃቤ ህግ ወገንተኝነት ያሳያል ብለን ስለምናምን ችሎቱ እንዲቀየርልን የጠየቅነው አቤቱታ ላይ ብይን ሳይሰጥ ጉዳያችንን ችሎቱ እንዳያይ ይደረግልን›› ሲል ተናግሯል፡፡ ችሎቱ አቤቱታው ለምን ለፕሬዝዳንቱ እንደቀረበ ግልጽ እንዳልሆነለት በመግለጽ አቤቱታው ለራሱ ለችሎቱም እንዲደርሰው ጠይቆ ከተከሳሾች እንዲደርሰው አድርጓል፡፡
በሌላ በኩል 4ኛ ተከሳሽ አቶ ደሴ ካህሳይ የትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪ መሆናቸው ታውቆ አስተርጓሚ እንዲመደብላቸው ጠይቀው እንደነበር በመግለጽ እስካሁን አስተርጓሚ እንዳልተመደበላቸው ገልጸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት በሚል ለየካቲት 4/2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀውን ግንቦት ሰባት የተባለ የፖለቲካ ድርጅት ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ ሲያመሩ ማይካድራ የተባለ የድንበር ከተማ ላይ መያዛቸውን አቃቤ ህግ በክሱ ላይ አስፍሯል፡፡

ሰውየው ---ብርሃኑ ነጋ ( ሄኖክ የሺጥላ )

#‎በሄኖክ_የሺጥላ‬
ሰውየው ---ብርሃኑ ነጋ ( ሄኖክ የሺጥላ )
አጭር ፍቅር
ሰውየው ሕልም አለው ። የአንደበቱ ርትዖነት ካለው የቃላት አጠቃቀም እና ልቀት ሳይሆን የሚመነጨው ከሃሳቡ ጠጣርነት እና ከቆመለት ትልቅ እውነት እንጂ !
ሰውየው ሕልም አለው ፣ ለዚያውም በሞቀ ቤት እና በቀዘቀዘ ቢራ ውስጥ በሚደረግ የሳይበር ጦርነት የሚጸና ሳይሆን ፣ የማሽላ እንጀራ እየበላ አፈር ላይ እየተኛ ፣ ከእባብ እና ገጊንጥ ጋ እየተታገለ ፣ በሞርታር እና በፈንጂ ወረዳ ውስጥ ውድ ነብሱን አቁሞ የሚሞትለት እጹብ ሕልም ።...
ሰወየው ትሁት ነው ፣ የትልቅነት ሚስጥሩ ምን እንደሆነ የገባው ትሁት ። ሕልሙ ባለ ወፍራም ቆዳ ያደረገው እንደራሴ ፣ አላማው ለትንንሽ ነገሮች እና በትንንሽ ነገሮች ከማኩረፍ እና ከመኮፈስ ነጻ ያወጣው የኔ ዘመን በትረ አሮን ። በግልምጫ እና በእርግጫ ፖለቲካ ውስጥ ሊባክን የሚችል ታል-ኢት ( የሰኮንድ ግማሽ ) የሌለው ሰው ። ሰውየው አፋር ነው ሃገሩ ፣ ጎጃሜም ነው ፣ በኦሮሞነቱ አይታማም ፣ ጥርት ያለ ጉራጌ ነው ፣ ዘሩን የቆጠሩ ሱማሌ ስለመሆኑ ይናገራሉ ፣ አብረውት ያደጉት እና በቅርብ የሚያውቁት ስለመንዜነቱ የሚያውቁትን ሁሉ ሳይደብቁ ያወራሉ ፣ እርግጥ ሰውየው ኢትዮጵያዊ ነው ። ማነስ አይችልም ፣ በጎጥ እና በጎሳ ፣ በአውራጃ እና ወረዳ ፣ ተቆርሶ እና ተሰባብሮ የሚነገር ማንነትም ሆነ ፣ የሚቆጠር ደም የለውም ። ሕሉሙ ከደሙ ጋ አንድ አይነት ነው ፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊ እና ዘረ ኢትዮጵያዊ ፣ ሰወየው !
ስለ ሰውየው ሳስብ ኩራት ይሰማኛል ፣ ምክንያቱም ኢትዮጵያዊነት እንደማይሞት ምሳሌ ሆኗልና ፣ ቃሉን አላጠፈምና ፣ የሚኖርለት ሰው ባይኖር እንኳ የሚሞትለት ክብር እና ነጻነት ያለው ስለሆነ ። በቅርቡ ዋሽንግተን ዲስ ባደረገው ንግግር " እዚህ ውስጥ ብዙ የማውቃችሁ ጓደኞቼን ወዳጆቼን አይቻለሁ ፣ ሁሌ አስባችሗለሁ ፣ ላናንተ ብዬ ግን ከምሄድበት አልቀርም " የምትለዋን ሐረግ ድግሜ ደጋግሜ አደመጥኩ ፣ በእድሜ የሱ እኩዮች የሆኑ ፣ እንደሱ ወይም ከሱ በላይ የተማሩ ፣ ሀገር ሀገር የሚሉ ግን አንዳች ቁም ነገር ያለው ሥራ መስራት ያልቻሉት ወዳጆቹ ምን ይሰማቸው ይሆን ? እነዚህ በጥላቻ እና በማጥላላት የፖለቲካ ቁማር የሰከሩ << የፖለቲካ ቁሞ ቀሮች >> ወይም ዊዶዎች ይህንን ሲሰሙ ምን ይሉ ይሆን ?
እርግጥ ይህንን ጽሑፍ የምታነቡ ሰዎች ማሽቃበጥ ሊመስላችሁ ይችላል ። እርግጥ አልተሳሳታቹም እያሽቃበጥኩ ነው!! ሰው እንኳን ለብርሃኑ ነጋ ለወያኔ ያሽቃብጥ የለ ። ታዲያ ምን ሽግር ኣለው ?
ሺዎች ከጎንህ ነን ። ከጎንህ ያቆመን ደሞ የቆምክለት አላማ ነው !

Wednesday, 3 February 2016

መለስ ሳይጠየቁ ሾለኩ

መለስ ሳይጠየቁ ሾለኩ
* በጋምቤላ የለኮሱት እሳት አሁንም እየነደደ ነው
* “የሟቾች ቁጥር እስከ መቶ ሊደርስ ይችላል” ነዋሪዎች
* “የሞቱት 14 ሰዎች ናቸው” ኢህአዴግ
ሰሞኑን በጋምቤላ በደረሰው የእርስበርስ ፍልሚያ እስከመቶ የሚጠጉ መሞታቸውን የክልሉ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ኢህአዴግ በበኩሉ የሞቱት 14 ብቻ ናቸው ይላል፡፡ ዘረኝነትንና ጠባብ ጎሰኝነትን ለኢትዮጵያ እንደ “ገጸ በረከት” ያመጡት መለስ በየቦታው የጫሩት እሣት ለፍርድ ሳያቀርባቸው ሾልከዋል፡፡ እሣቱ ግን አሁንም እየነደደ ነው፡፡
ጎልጉል ከአካባቢው ነዋሪዎችና ጉዳዩን በቅርብ ሲከታተሉ ባገኘው መረጃ መሠረት በግጭቱ የሞቱት እስከ መቶ እንደሚደርስ ይነገራል፡፡ ግጭቱ ከመነሻው በቀላሉ የተነሣ ቢሆንም ወዲያውኑ ወደከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ሥር የሰደደ ፖለቲካዊ ምክንያት እንዳለው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡ ይህንኑ ዜና ኢሳት ሲዘግብ የሟቾቹ ቁጥር ከመቶ እንደሚያልፍ ምንጮቹን ጥቅሶ አስታውቋል፡፡
ጸረ ቁጥር የሆነው ኢህአዴግ ወራትን ባስቆጠረው የተማሪዎች ዓመጽ ከሁለት መቶ በላይ ሞተው ሟቾች ከአስር ያልበለጡ ናቸው ከማለቱ በፊት መጀመሪያ ምንም የሞተ የለም፤ ቀጥሎም የሞቱት አምስት ናቸው ማለቱ ይታወሳል፡፡ አሁን ደግሞ የኢህአዴግ አፈቀላጤ ጌታቸው ረዳ በጋምቤላው ግጭት የሞቱት ቁጥሩን እርግጠኛ ለማስመሰል ይመስላል 14 ናቸው ብለዋል፡፡
አቶ መለስ በአዛዥነት ከሌሎች የህወሃት ሹማምንት ጋር በመሆን በሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ 424 የአኙዋክ ጎሣ አባላት በግፍ መጨፍጨፋቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የጭፍጨፋው አስፈጻሚ የነበሩት እና ኢህአዴግን ከድተው በውጪ አገር የሚገኙት የቀድሞው የክልሉ ኃላፊ ኦሞት ኦባንግ ኦሉም ከህወሃት ጋር ሆነው የተከሉት መርዝ ለሰሞኑ ግጭት መባባስ ምክንያት እንደሆነ ጉዳዩን የሚከታተሉ ወገኖች ይናገራሉ፡፡
በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) የዘር ጭፍጨፋ ከተካሄደባቸው በኋላ መሬታቸውን በግፍ ከተነጠቁት አኙዋክ ወገኖች መካከል ከዘር ማጥፋቱ ያመለጡት በበርካታ ሺዎች የሚቆጠሩት አገር ለቅቀው ተሰደዋል፡፡ በዓለምአቀፍ ድርጅቶች ዘንድ በቁጥር ደረጃ ለመጥፋት የተቃረቡ ከሚባሉት አኙዋኮች በህይወት የቀሩት ደግሞ አሁን ለዘር እንዳይቀሩ ሆነው እየተጨፈጨፉ ይገኛሉ፡፡ የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ግጭቱ እርስበርስ መሆኑ ነው፡፡
ከዚህ ሌላ ህወሃት ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ያለው “የጫጉላ ጊዜ” በማብቃቱ ለተቀናቃኛቸው ሬክ መቻር ግልጽ ድጋፍ እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አኳያ የኑዌር ተወላጅ የሆኑት ሬክ መቻር ወደ ጋምቤላ እንደፈለጉ ሲወጡና ሲገቡ መክረማቸውን ጎልጉል ከዚህ በፊት ዘግቦ ነበር፡፡ የመቻርን ኃይል ለመደገፍ ከጋምቤላ በርካታ ኑዌሮች ወደ ደቡብ ሱዳን ገብተው ከሳልቫ ኪር የዴንቃ አባላት ጋር ጦርነት መጋጠማቸውና ከሞቱት መካከልም “የመከላከያ ሠራዊት” አባላት ለመሆናቸው ማስረጃ ስለመገኘቱ ጉልጉል በተደጋጋሚ መረጃ ደርሶታል፡፡
አሁን በተከሰተው ግጭት ቀድሞውኑም የታጠቁት የኑዌር አባላት አሁን ደግሞ ከደቡብ ሱዳን ግጭት ጋር በተያያዘ የመቻር ኃይል ያስታጠቃቸው ድንበር እያለፉ በመዝለቅ በአኙዋኮች ላይ የሚያደርሱት ጥቃት አሁንም አልቆመም፡፡ የአኙዋክ ጎሣ አባላትም ራስን ከመከላከል ጀምሮ መልሶ እስከ ማጥቃት በሚያደርጉት ምት በገጠር ቀበሌዎች የሚገደሉት ንጹሃን ቁጥር እጅግ እየጨመረ መሄዱ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ለጎልጉል አስታውቀዋል፡፡
“ኢትዮጵያውያንን እንደ እህል በዘር ከረጢት እየሠፈረ ለዚህ ሁሉ ዓይነት ስቃይና መከራ እንዲሁም ለማያባራ የዘር ግጭት የዳረገው መለስ ነው፤ ወደ ህይወት ማምጣት ብችል አስመጥቼ ፍትህ እንዲበየን ማስደረግ እፈልግ ነበር፤ ሙት አይወቀስም ይባላል፤ ልክ ሊሆን ይችላል አባባሉ ግን ለመለስ አይሠራም፤ እኔ ፍትህ የጠማኝ ነኝ” በማለት የመረረ አስተያየቱን ለጎልጉል በውስጥ መስመር የሰጠው ወጣት ይናገራል፡፡
ህወሃትና መለስ በኢትዮጵያ የተከሉት የዘር ፖለቲካ በአገሪቱ በበርካታ ቦታዎች የማንነት ጥያቄ ከማስነሳት አልፎ የህይወት መስዋዕትነት እያስከፈለ ነው፡፡ እምቢባዮችን “ልክ እናስገባለን” በማለት እየፎከረ አገር በነጻ አውጪ ስም የሚገዛው ህወሃት፤ የህይወት ዑደቱን እስኪያጠናቅቅ “ባለ ራዕዩ መለስ” ያስቀመጡለትን “ራዕይ” በትጋት እያስፈጸመ ይገኛል፡፡
(http://www.goolgule.com/

Tuesday, 2 February 2016

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
ከአስመራ ወደ አሜሪካ ለአጭር ጊዜ ለሥራ ጉዳይ መጥተዋል የሚለውን ተከትሎ ካሁን በኋላ አይመለሱም ለሚለው አሉባልታ ምላሽ ሰጥተዋል:: ፕሮፌሰር ብርሃኑ እንዳሉት ከዚህ ‘ሲያምራችሁ ይቅር እኔ ከአሁን በኋላ ከዚህ ትግል አልርቅም” ብለዋል::“የብሔር ጥያቄን የመለሰች፤ ከራሷ ጋር የታረቀች ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን”– ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ ባደረጉት ሕዝባዊ ስብሰባ በኢትዮጵያ በተከሰተው ረሃብ; በኦሮሞ ተማሪዎች አመጽ እና ትግሉ ስላለበት ሁኔታ እንዲሁም ስለተቃዋሚዎች ተናግረዋል::
...
በኢትዮጵያ የተከሰተው ረሃብ የስርዓቱ ችግር ነው ካሉ በኋላ እርሳቸው የሚመሩት ተቋም ከዚህ ቀደም የገመተው የተራቢዎች ቁጥር አሁን ተግባራዊ እየሆነ እንደሆነ እንዲሁም ይህ አስተዳደር ከቀጠለ ከዚህ ቀደም እንደገመቱት በ2050 ዓ.ም 50 ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚራብ ገልጸዋል::
በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ዙሪያም እንዲሁ የተናገሩት ፕሮፌሰሩ በኦሮሚያ ክልል ህፃናት እና ነብሰጡርን ሳይቀር እየገደለ ያለውን ስርዓት ሕዝቡ እየሞተ ያለው ወገኔ ነው ብሎ ማውገዝ አለበት ብለዋል:: በተለይም በአሁኑ ወቅት ከኦሮሞ ድርጅቶች ጋር በህብረት ለመታገል ንግግሮች መጀመራቸውንም አስታውቀዋል::
ስለተቃዋሚዎችም የተናገሩት ፕሮፌሰሩ “የተቃዋሚዎች የምኞት ፖለቲካ ነው የሚከተሉት” ሲሉ ተችተው የምር መታገል እንዳለባቸው አስምረውበታል::
ወቅታዊውን የአርበኞች ግንቦት 7 ሁኔታ በተመለከተም “ወታደሮቻችን ያሉት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው… ትግላችንን ለመቀላቀል ካሁን በኋላ ለምትፈልጉ ወደ ሰሜን ብቻ መሄድ የለባችሁም” ብለዋል::

Sunday, 31 January 2016

በሰሜን ጎንደር የወያኔ አፈና ቀጥሏል

ዛሬም በሰሜን ጎንደር የወያኔ አፈና ቀጥሏል ‪#‎AmharaProtests‬
‪#‎ETHIOPIA‬ | ህወሃት መራሹ የወያኔ ቡድን በሰሜን ጎንደር ሽንፋ እና አካባቢው ላይ የሚገኙ በህብረተሰቡ ተሰሚነት ያላቸውን የአማራና ቅማንት ማህበረሰብ አካል የሆኑ ሰዎችን እያፈነ ወደ ማጎሪያ ቤቶቹ ማጋዝ ቀጥሏል፡፡
ታሳሪዎቹ ለዕስራት የተጋለጡበት ምክንያት የኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከለላውን አንቀበልም ልንዋጋው ይገባል በማለታቸው እና በተጨማሪ አማራና ቅማንት ማህበረሰቦች ላይ እየሰራ የሚገኘውን የወያኔ ሴራ ለህብረተሰቡ እያጋለጡ በመሆኑ እንደሆነ ከቦታው የመረጃው ምንጮቻችን ገልጸውልናል፡፡
ከታፈኑት ሰዎች መካከል
-መ/አለቃ ደጀኔ ወርቁ
-አቶ አታላይ ደምሴ
-አቶ ጋሹ ጌጡ
-አቶ ነጋ አቤ፥አቶ አስቻለው እና ሌሎች በርካቶች ይገኙበታል፡፡
©

Wednesday, 20 January 2016

አቶ ኦባንግ የኢህአዴግ ደጋፊ ስደተኞችን አስጠነቀቁ

 ኦባንግ የኢህአዴግ ደጋፊ ስደተኞችን አስጠነቀቁ “በአስመሳይ ስደተኞች ላይ በቂ መረጃ አለ” “ክፉን በክፉ መመከት ባያስደስትም ወቅቱ ያስገድደናል” ሲሉ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር ኦባንግ ሜቶ በተለይ ለጎልጉል ተናገሩ። አገዛዙን ሸሽተው በተለያዩ አገራት ከለላ አግኝተው በስደት የሚኖሩም ሆኑ ጉዳያቸው እየታየ ያሉ ወገኖች አካሄዳቸውን እንዲያስተካክሉ አስጠንቅቀዋል።
የአሜሪካ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ህግ አውጪዎች፣ የጀርመን የኢሚግሬሽን ሃላፊዎችና ከፍተኛ የፖለቲካ ሰዎች፣ ከኖርዌይ የኢሚግሬሽን ጉዳይ ሃላፊዎችና ተዛማጅ ሃላፊነት ካላቸው የህግ ክፍሎች፣ በካናዳ በተለያዩ ደረጃ ካሉ ባለስልጣናትና ወትዋቾች (አክቲቪስቶች)፣ በስዊድን አንዲሁም በእንግሊዝ በተመሳሳይ ግንኙነት ፈጥረው እየሰሩ መሆኑንን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አገራቱ የስደት ፈቃድ ካገኙ በኋላ ለስደት ዳረገን ከሚሉት መንግሥት ጋር በቅርብ እየሰሩ ስላሉ አስመሳይ ስደተኞች አስገራሚ መረጃዎች መሰብሰባቸውን አውቃለሁ” ብለዋል።
አቶ መለስ በሞቱ በወር ጊዜ ውስጥ ብቻ በካናዳ ቫንኮቨር 27 አንድ አይነት ቋንቋ ብቻ የሚናገሩ ወጣቶች ጥገኛነት መጠየቃቸውን ጉዳዩን በጥብቅ እየመረመሩት ካሉ ክፍሎች ማረጋገጣቸውንና የምርመራውን ውጤት በመጠባበቅ ላይ እንደሚገኙ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ “ወጣቶቹ ካናዳ የገቡት ለእያንዳንዳቸው 75 ሺህ ዶላር በማውጣት ነው። ይህን ገንዘብ ማን ሰጣቸው? እንዴት አገኙት? እንዴት ከአንድ አካባቢ (ክልል) ብቻ ሊሆኑ ቻሉ? የሚሉት ጉዳዮች ምርመራውን በያዙት ወገኖች ላይ ግራሞት የፈጠረ ትልቅ ጉዳይ ነው” በማለት የጉዳዩን አሳሳቢነት ከገንዘብ ማሸሽ ጋር በማያያዝ አመላክተዋል። ለምሳሌ አንድ ጉዳይ አነሱ እንጂ በመላው ካናዳ በተመሳሳይ የምርመራ ስራ እየተሰራ መሆኑንን ተናግረዋል።
የካናዳው አንድ ማሳያ ሲሆን በአሜሪካ ግዙፍ ቪላዎችን እየገዙ ያሉት ክፍሎች ጉዳይ ከገንዘብ ማሸሽ ጋር ተያይዞ እየተመረመረ እንደሆነ አቶ ኦባንግ አስረድተዋል። ጥገኝነት ካገኙ በኋላ “ሊገለን ሲል አመለጥነው” ያሉትን ኢህአዴግን የሚደግፉ ክፍሎች ላይም ለሚመለከታቸው ባለስልጣናትና ተቋማት ከሚቀርበው መረጃ በተጨማሪ ከፍትህ ወዳድ ተጽዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ጋር ድርጅታቸው በጥምረት እየሰራ መሆኑን አቶ ኦባንግ አልሸሸጉም፡፡
በጀርመን ኑረንበርግ በኢሚግሬሽን ጉዳዮች ዙሪያ የሚሰሩ ባለስልጣናት በተመሳሳይ የምርመራ ስራ እያከናወኑ እንደሆነ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ፣ በግል በጉዳዩ ዙሪያ መነጋገራቸውን አስታውቀዋል። የጥገኝነት ፈቃድ ካገኙ በኋላ ዲያስፖራውን በመከታተልና አገር ቤት የሚገኙ ቤተሰቦቻቸው ለችግር እንዲዳረጉ የሚያደርጉትን ክፍሎች ማንነት ነቅሰው እንደሚያውቋቸው ባለሥልጣናቱ በግንኙነታቸው ወቅት እንዳረጋገጡላቸው አመልክተዋል።
“ኢህአዴግ ለጊዜው የጠመንጃ ሃይል አለው። የገንዘብ አቅም አለው። ወዳጆችም አሉት። እኛ ደግሞ በየአቅጣጫው ፍትህ ወዳድ አጋሮች አሉን። ከነሱ ጋር እየሰራን ነው” በማለት አስረግጠው የተናገሩት ኦባንግ በማንኛውም መስፈርት ስደት ላይ ያሉ ወገኖችን መከታተልና መሰለል ተቀባይነት የለውም ብለዋል።
“አሜሪካ፣ ካናዳ፣ ኖርዌይ፣ እንግሊዝ፣ ስዊድንና ጀርመን አገር ባለስልጣናቱ ከበቂ በላይ መረጃ አግኝተዋል። እኛም እየሰራንበት ያለ ተከታታይ ስራ አለ። በየአቅጣጫው የሚደረገው ትግል በቅርቡ ፍሬው መታየት ይጀምራል” የሚሉት ኦባንግ ርምጃው መወሰድ ሲጀምር ከስድስት እስከ አስራ ሁለት ዓመት እስር እንደሚያስከትል፣ ከዚያም የከፋ አደጋ እንዳለው ጠቁመዋል።
በትምህርትና በተለያዩ ስልጠናዎች ወደ ተለያዩ ዓለማት የሚሰማሩ የአገዛዙ አገልጋዮችም ቢሆኑ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባቸው የሚያሳስቡት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ዋና ዳይሬክተር “አገዛዙ መድቧቸው በየኤምባሲው ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች፣ የስለላ ሰዎች፣ ከፍተኛ ባለስልጣናት ምስላቸውንና ማንነታቸውን ባደባባይ አይገልጹም። በኤምባሲዎች ድረ ገጽ ላይ እንኳ ስለማንነታቸው በቂ መረጃ ለመስጠት ድፍረት የላቸውም። የስርዓቱ ባህሪና የወንጀለኛነቱ መጠን ራሳቸውን እንዲገልጹ አይፈቅድላቸውም” በማለት በተራ መደለያና ጥቅማ ጥቅም ደረታቸውን እየሰጡ ያሉ ወገኖች አካሄዳቸውን በመመርመርና የሚያስከብራቸውን ተግባር እንዲፈጽሙ ጥሪ አስተላልፈዋል።
“ምክር በመለገስ ሰፊ ጊዜ የወሰድነው ክፉን በክፉ የመመለስ እምነት፣ ክፉ እንድናደርግ የሚገፋን ድርጅታዊ አቋም ስለሌለንና የሚጠሉንን ጭምር ነጻ የሚያወጣ ግዙፍ ራዕይ ስላለን ነው” የሚል ጥልቅ አስተያየት የሰነዘሩት አቶ ኦባንግ፣ በአገራቸው መኖር ያልቻሉ ወገኖች ተሰደውም ሰላም ሲያጡ መመልከት ግን የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን አመልክተዋል። ከዚህም በተጨማሪ እሳቸው በግል፣ ድርጅታቸው በመርህ የሚታገሉለት የሰዎች መብት መከበር ብሩህ አጀንዳ በዝምታ እንዲቀመጡ እንደማይፈቅድላቸው ተናግረዋል።
ከኖርዌይ የኢሚግሬሽን ባለስልጣናት ጋር በተገናኙባቸው ወቅቶች ይህንኑ ጉዳይ አስመልክቶ በግልጽ እንደነገሯቸው ያመለከቱት ኦባንግ ሜቶ፣ አሁን ስሙንና ዝርዝር ጉዳዩን ለመናገር ፈቃደኛ ካልሆኑት ክፍል ጋር በጋራ እየሰሩ መሆኑንን ጠቁመዋል። አኢጋን ያቋቋመው የግልጽነትና የተጠያቂነት ግብረ ሃይል አንዱና ትልቁ ስራው እንዲህ ያሉ ጉዳዮችን መርምሮና አጣርቶ ለሚመለከታቸው በማቅረብ ፍትህን መጠየቅ መሆኑንን ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ዝርዝሩን መናገር ቢከብድም ብዙ ስራ እየሰራንበት ያለው የስደተኞች ጉዳይ የሌሎችንም ተሳትፎና ትብብር ይጠይቃል” ብለዋል።
“በስሜት መታገል አያዋጣም” የሚል የትግል ማስተካከያ ሃሳብ ፈንጠቅ ያደረጉት አቶ ኦባንግ የስደት ማመልከቻቸው ተቀባይነት አግኝቶ የመኖሪያ ፈቃድ ካገኙ በኋላ አገር ቤት በመመላለስ፣ ህግ በመተላለፍ ለአገዛዙ የሚሰሩ በሙሉ “ብልጥና አዋቂ ነን፣ ባለጊዜዎች ነን” በሚል አስተሳሰብ የሚንቀሰቀሱ አንደማያዋጣቸው ሲያሳስቡ “ለእንደዚህ አይነቶች ሁሉም ዓይነት መንገድ አይሰራላቸውም። ግለሰቦችንና ባለስልጣናትን ሳይሆን አሰራርን በማጭበርበር ይጠየቃሉ። አገራቱ እንደ ኢትዮጵያ ሳይሆን ስራ ላይ የሚውል ህግ አላቸውና ይተገብሩባቸዋል። አሰራራቸው ሲጭበረበር ዝም የማይሉት ለማንም ሲሉ ሳይሆን ለራሳቸው ሲሉ ነው። አሰራር / ሲስተም/ ሲበረዝ የሚያስከትለውን አደጋ ስለሚረዱ የሚታገሱ ካልሆነ በቀር በዝምታ አያልፉም። በኖርዌይም ሊሆን የታሰበው ይህ ነው። አሁንም ዝርዝር መረጃ ለመስጠት እቸገራለሁ” በማለት ነው። አቶ መለስ ህይወታቸው ባለፈ ወቅት በስደት ካምፕ የሚኖሩ ጭምር ለቅሶ መቀመጣቸው በኖርዌይ ሚዲያዎች አስገራሚ ተብሎ መዘገቡ፣ በህዝቡና በፖለቲከኞች ዘንድ መነጋገሪያ አጀንዳ እንደነበር አይዘነጋም።
በርካታ አሳዛኝና ህሊናን የሚፈታተኑ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሆነ ያወሱት ኦባንግ ሜቶ፣ ህጻናትን በጉዲፈቻ ስም በመቸብቸብ፣ ሴት እህቶቻችንን አረብ አገራት ያለ ዋስትና በመላክ ከፍተኛ ገበያ እየሰሩ ያሉት የህወሃት ሰዎች እንደሆኑ በበርካታ ማስረጃዎች መረጋገጡን ያስታውሳሉ። አያይዘውም አገራቸውን ለቀው ለስደት የሚወጡትን ወደ ኬኒያ፣ ታንዛኒያና ደቡብ አፍሪካ ብሎም በጅቡቲና በሶማሌ በኩል ገንዘብ እያስከፈሉ የሚያሻግሩት አሁንም እነሱ ናቸው ሲሉ አስቀድመው ስለ ጠየቁት ትብብር ማሳሰቢያቸውን ያጠናክራሉ።
“በማስተዋል እንስራ” የሚሉት ኦባንግ በየአቅጣጫው መረጃ ላይ የተኙና፣ በምን አገባኝ ስሜት ዝምታን የመረጡ ወገኖች ያላቸውን መረጃ በመስጠት የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ከተለያዩ አካላት ጋር እየሰራ ያለውን ስራ እንዲያግዙ አሳስበዋል። ይህንን ማድረግ አቶ ኦባንግንና እርሳቸው የሚመሩትን ድርጅት መርዳት ሳይሆን ራስንና አገርን መርዳት እንደሆነም አጽንዖት ሰጥተው ተናግረዋል።
ከተቋቋመ 135ዓመታትን ያስቆጠረው የአሜሪካ ሕግ ባለሙያዎች ማኅበር (ABA) እየተባለ በሚጠራውና 400 ሺህ በላይ አባላት ባሉት የህግ ባለሙያዎች ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ከሁለት ሳምንት በፊት ንግግር እንዲያደርጉ በተጋበዙበት ወቅት አቶ ኦባንግ ሜቶ በርካታ ጉዳዮችን በማንሳት ድጋፍ ጠይቀው አዎንታዊ ምላሽ እንዳገኙ ጠቅሰዋል፡፡ በርካታ የህግ ባለሙያዎች በተገኙበት ስብሰባ ላይ በኢትዮጵያ ያለውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ ኢህአዴግ ህግን ከለላ በማድረግ በዜጎች ላይ የሚፈጽመውን ወንጀል፣ ለእንደዚህ ዓይነት ተግባሩ ማስፈጸሚያም የጸረ ሽብርተኝነትን፣ የመያዶችን፣ ወዘተ ህጎች በማውጣት ዜጎችን ለእስር፣ ለስደት፣ ለስቃይ መዳረጉን፣ የፍትህ አካላቱን ህግን በሚያከብሩና ፍትህ በሚያስፈጽሙ ሳይሆን ራሱ በመሠረተው ተቋም እያመረተ ለፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረገ መሆኑን፣ ከዚህ አልፎ ደግሞ በስደተኛነት ስም ደጋፊዎቹን ወደ ውጪ በመላክ በሃሰት የኢህአዴግ ሰለባ በማስመሰል በየምዕራቡ ዓለም የመኖሪያ ፈቃድ እንዲያገኙ በማስደረግ መልሶ ስደተኛውን እዲሰልሉና ለሥርዓቱ እንዲሰሩ እያደረገ መሆኑን፣ ወዘተ በስፋት አብራርተዋል፡፡ የባለሙያዎቹ ማኅበር ጉዳዩን በጥልቀት እንደሚያየውና ያለውን ከፍተኛ የሰው ኃይል በመጠቀም ከአኢጋን ጋር እንደሚሰራ ከሌሎች ማኀበራት ጋር በመሆንም በተለይ በምዕራቡ ዓለም የተሰገሰጉትን አስመሳይ ስደተኞች ወደ ፍትህ የማምጣቱ ጉዳይ ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ለአቶ ኦባንግና ለድርጅታቸው አረጋግጠዋል፡፡

Tuesday, 19 January 2016

አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ተቋርጠው የነበሩት ከ80 በላይ የሚሆኑ ክሶች እንደገና እንዲታዩ ተወሰነባቸው

ኢሳት (ጥር 09 ፥ 2008)
ከመንግስት ጋር ያደረጉት ስምምነት ተከትሎ በቅርቡ ወደሃገር የተመለሱትና ከቀናት በፊት ለእስር የተዳረጉት የአክሰስ ሪል ስቴት መስራች የተቋረጡባቸው ከ 80 በላይ ክሶች እንደገና እንዲታዩ ተወሰነ።
የኩባንያው መስራችና አመራር አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ወደሃገር ከተመለሱ በኋላ ሊተገብሩ ቃል የገቡትን ስራ ባለማከናወናቸው ምክንያት ክሳቸው እንዲቀጥል መደረጉን የፍትህ ሚኒስቴር ገልጿል።
ከመንግስት ጋር ድርድር አድርገው ባለፈው አመት ወደሃገር ቤት የተመለሱት የአክሰስ ሪል ስቴት መስራች፣ ወደሃገር ሲመጡም ያለመታሰር ዋስትና አልተሰጣቸውም ነበር ሲሉ የፍትህ ሚኒስትሩ አቶ ጌታቸው አምባዬ መግለጻቸው ከሃገር ቤት የተገነው መረጃ አመልክቷል።
የገቡትን ቃል መፈጸም አልቻሉም የተባሉ አቶ ኤርሚያስ ባለፈው ሳምንት በቁጥጥር ስር መዋላቸው የሚስታወስ ሲሆን፣ ክስ ተመስርቶባቸው የነበሩ እና የተቋረጡ ከ80 በላይ ክሶችም እንደገና የሚታዩ ሚኒስትሩ አስታውቀዋል።
አክሰስ ሪል ስቴስ ከስድስት አመት በፊት ከሁለት ሺ በላይ ከሚሆኑ ደንበኞች ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ ወደስራ ቢገባም ለደንበኞቹ መኖሪያ ቤትን አላስረከበም በሚል ብውዝግብ ውስጥ መቆየቱ ይታወቃል። አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በበኩላቸው ቤቶቹን ሰርቶ ለማስረከብ የገጠማቸው መሰናክልም መግለጻቸው ይታወሳል።


በሆሳዕና ከተማ የህዝብ ትራንስፖርት ማመላለሻ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ ተቋረጠ


ኢሳት (ጥር 09 ፥ 2008)
በሆሳዕና ከተማ ከመንጃ ፈቃድ ቅጣት እና አስተዳደር ብልሹነት ጋር በተያያዘ የህዝብ የትራስፖርት ማመላለሻ አገልግሎት ለሁለት ቀን ተቋርጦ መዋሉት ዛሬ ሰኞ ለኢሳት የደረሰው መረጃ አመለከተ።
አንድ ሆሳዕና ወደሌላ ወረዳ ወይም ከወደ ዋና ዋና ከተሞች የሚያጓጉዙ የትራንስፖት መገናኛ አገልግሎቶች በመቋረጣቸው ህዝቡ ከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር ውስጥ ላይ እንደሆነ አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ በሆሳዕና የሚኖሩ ሰው ለኢሳት በስልክ ተናግረዋል።
“መንግስት ያወጣው አዲሱ ህግ አንድ ሹፌር 3 ጊዜ አንድ አንድ ሺ ብር ከተቀጣ መንጃ ፈቃዱን ይነጠቃል የሚለው ነው አድማውን ያስነሳው” ያሉት አንድ አስተያየት ሰጪ፣ አድማውን ተላልፎ ከቡታጅራ ሆሳዕና ይጓዝ የነበረ አንድ ሃይሩፍ የትራስፖርት ተሽከርካሪም ወራቤ ላይ በትራንስፖርት አገልግሎት ሰራተኞች እና በህዝቡ እንደወደመ ተነግሯል።
አዲሱን የመንግስት መመሪያ በመቃወም የሆሳዕና፣ ጉራጌ  እና ወላይታ ዞኖች ባሉት ከተሞች የሚኖሩ ነዋሪዎች በአድማው መሳተፋቸው ታውቋል።
የአካባቢው ህብረተሰብም ታምቀው የቆዩ የመልካም አስተደደር ችግሮችን እየገለጸ ያለበት አጋጣሚ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች ለኢሳት አስታውቀዋል።
ትናንት እሁድና ዛሬ ሰኞ ከባጃጅ ጀምሮ ሁሉም የትራስፖርት አገልግሎቶች በመቋረጣቸው፣ ከከተማዋ የሚወጣም ሆነ የሚገባ ምንም አይነት የትራስፖርት አገልግሎት ተሽከርካሪ እንደሌለ ታውቋል።
ከአድማው ጋር በተያያዘ በሃድያ ዞን ማረሚያ ቤት 4 ሰዎች በመንግስት ሃይሎች መታሰራቸው ተነግሯል።
የመንግስት አዲሱን አሰራር በመቃወም ነገ ማክሰኞ በሆሳዕና ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ እንደተጠራ በአካባቢው የሚኖሩ ሰው ለኢሳት ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ በህጻናት ላይ ከጦርነት ጋር ተመሳሳይነት ያለው ጉዳት እያደረሰ ነው ተባለ


ኢሳት (ጥር 09 ፥ 2008)
በኢትዮጵያ እየተባባሰ የመጣው የድርቅ አደጋ በህጻናት ላይ የሚያደርሰው ጉዳት ጦርነት በሶሪያ ህጻናት ላይ እያደረሰ ካለው አደጋ ጋር ተመሳሳይ እየሆነ መምጣቱን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቁ።
ይኸው በስድስት ክልሎች ጉዳትን እያደረሰ ያለው የድርቅ አደጋ ከ 400ሺ በላይ በሚሆኑ ህጻናት ላይ ክፉኛ የአካልና የጤና ችግርን እያስከተለ እንደሚገኝ ድርጅቱ ገልጿል።
ድርቁ በህጻናት ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት ጦርነት በሶሪያ ህጻናት ላይ እያደረሰ ካለው ጉዳት ጋር ተመሳሳይ መሆኑን ያስታወቀው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የህጻናቱን ህይወት ለመታደግ አፋጣኝ ርብርብ እንደሚያስፈልግ አሳስቧል።
በኢትዮጵያ ጉዳትን እያደረሰ ያለው የድርቅ አደጋና በሶሪያ ቀጥሎ የሚገኘው ጦርነት በአለማችን ግንባር ቀደም የሰብዓዊ እርዳታን የሚፈልጉ አስቸኳይ ችግሮች ሆነው ተገኝተዋል ሲሉ የህጻናት አድን ድርጅት ተወካይ የሆኑት ካሮሊን ማይልስ ገልጸዋል።
ለዚሁ አፋጣኝ የነብስ አድን ስራም የህጻናት አድን ድርጅት ወደ 100 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ እንደሚፈልግ ተወካዩ ይፋ ማድረጋቸውን ኒውስ 24 የተሰኘ ጋዜጣ ዘግቧል።
ድርቁ ዱዳትን እያደረሰ በሚገኝባቸው አካባቢዎች ዘገባን ያቀረበው አልጀዚራ የቴሌቪዥን ጣቢያ በበኩሉ አለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማት ለምግብ እርዳታ የተጋለጡ ሰዎች በቂ እርዳታን እያገኙ እንዳልሆነ መግለጻቸውን አስነብቧል።
በድርቁ ሳቢያ ክፉኛ ጉዳት የደረሰባቸው እና የአስር ልጆች አባት የሆኑት ሞሃመድ ዱባሃላ ከነበራቸው 53 ላሞች መካከል አምስቱ ብቻ መትረፋቸውን ለቴለቪዥን ጣቢያው አስረድተዋል።
በተለይ ህጻናት ላይ እያደረሰ ባለው ጉዳት ሃዘን እንደተሰማቸው የገለጹት አርብቶ አደሩ ከመንግስት እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ አለመሆኑን ተናግረዋል።
በቀጣዮቹ ሁለት ወራት በድርቁ ሳቢያ አስቸኳይ የምግብ ድጋፍን የሚፈልጉ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችልና የድርቁ ጉዳትም እየከፋ እንደሚሄድ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አሳስቧል።

ኢትዮጵያ አልፋሽጋ የሚባለው ግዛት የሱዳን መሆኑን እንደምትቀበልና ለማስረክብ መቁረጧ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተናገሩ

“የሱዳን መሬት በኢትዮጵያ መያዙን የኢትዮጵያ መንግስት አምኖአል” ሲሉ የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ገለጹ
ጥር ፱ (ዘጠኝ) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኢብራሂም ጋንዱር ለአልጀዚራ እንደተናገሩት “ኢትዮጵያ አልፋሽጋ የሚባለው ግዛት የሱዳን መሆኑን እንደምትቀበልና ለማስረክብ መቁረጧን” ተናገሩ።
ለሱዳን ይሰጣል የተባለው መሬት 250 ካሬ ኪሎሜትር ስፋት ያለው ሲሆን፣ ለም የሆነ መሬትና በርካታ የውሃ ተፋሰሶች ያሉት ነው።
...
የሱዳን መንግስት የኢትዮጵያ አርሶአደሮች መሬቱን ሰጥቷቸው ሲያርሱት ነበር ያሉት ባለስልጣኑ፣በዚህ አመት ውስጥ መሬቱን ኢትዮጵያ ለሱዳን ልታስረክብ መሆኑን ተናግረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ንግግር፣ አቶ ሃይልማርያም ደሳለኝ በቅርቡ የሰጡትን መግለጫ የሚያጠናክር ነው። አቶ ሃይለማርያም የኢትዮጵያ ባለሃብቶችና አርሶአደሮች ወደ ሱዳን ገብተው እያረሱ መሆኑንና የኢትዮጵያ መንግስት የሱዳንን መንግስት ለምኖ እስካሁን በቦታው ላይ እንዲቆዩ ማድረጉን ተናግረው ነበር።
የሱዳን መንግስት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሰጡት መግለጫ ከኢትዮጵያው ጠ/ሚኒስትር ጋር መመሳሰሉ የተጠቀሰው መሬት ለሱዳን እንደሚሰጥ ማረጋገጫ ነው። በድንበሩ አካባቢ ያሉ የኢትዮጵያ አርሶአደሮች ግን መሬቱ የኢትዮጵያ መሆኑን ይናገራሉ።
የኢህአዴግ መንግስት መሬቱ የሱዳን መሆኑን አምኖ ከተቀበለ ቀሪው ነገር አለማቀፋዊ ህጋዊነትን ማላበስ ነው የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች፣ ሁለቱም መንግስታት ተስማምተው ስምምነታቸው ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከገለጡ፣ መሬቱን መልሶ ለማግኘት ጉዳዩን ውስብስብ ሊያደርገው ይችላል።
የመንግስት ቃለአቀባይ ጌታቸው ረዳ እና ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ የድንበር ጉዳይን ለማየት የተቋቋመ ኮሚቴ እንደሌለ፣ መሬት ለመስጠት ምንም ዝግጅት እንደሌለ ሲገልጹ ቆይተዋል። ይሁን እንጅ የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በመሪዎች ደረጃ ኮሚቴ ተቋቁሞ ጉዳዩ እየታየ መሆኑን ገልጸዋል። የኮሚቴው ሰብሳቢ አብደላ አል ሳድቅ ኮሚቴው ስራውን ያለምንም ችግር እያከናወነ መሆኑን ሱዳን ትሪቢዩን ዘግቧል።
የኢሳት ምንጮች እንደገለጹት ላለፉት ሁለት ወራት የደህንነት መስሪያ ቤት (ኢንሳ) መሬቱን የአየር ላይ ፎቶ ሲያነሳ ከርሟል። የአካባቢው ነዋሪዎች ለሚያነሱት ጥያቄ የደህንነት መስሪያ ቤቱ “የመሬቱ ልኬቱ የሚካሄደው ለልማት የሚውለውን መሬት ለመለየት ነው” የሚል መልስ ሲሰጥ ቆይቷል። የደህንነት መስሪያ ቤቱ መሬቱን የማስረከብ ሃላፊነት መውሰዱን ምንጮች ገልጸዋል።

Tuesday, 12 January 2016

የኖርዌይ ኤምባሲ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው ተቃውሞ በማገርሸቱ ዜጎች የጥንቃቄ እርምጃን እንዲወስዱ አሳሰበ

ኢሳት (ጥር 3 ፥ 2008) መቀመጫውን በኢትዮጵያ ያደረገ የኖርዌይ ኤምባሲ በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ዳግም በማገርሸቱ ምክንያት ዜጎች በክልሉ በሚያድርጉት ጉዞ ላይ የጥንቃቄ እርምጃን እንዲወስዱ አሳስቧል። የኢትዮጵያን የሰብዓዊ መብት ሁኔታ በቅርበት የምትከታተለው ኖርዌይ እየተካሄደ ያለው ተቃውሞ የጸጥታ ስጋት ሊሆን እንደሚችል አስታውቋል። የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባለስልጣናት በቅርቡ ለኤምባሲ ተወካዮች በሰጡት ማብራሪያ ተቃውሞው በቁጥጥር ስር ዉሏል ሲሉ ምላሽ መስጠታቸው ይታወሳል። ይሁንና በሁለቱ ወገኖች መካከል የተካሄደው ውይይት ተከትሎ ኖርዌይ ተቃውሞው አለመብረዱንና የጸጥታ ስጋት እየሆነ መምጣቱን በይፋ ስትገልጽ የመጀመሪያ ሃገር ሆናለች። መቀመጫቸውን በሃገሪቱ ያደረጉ የተለያዩ ሃገራት ተወካዮችና አለም አቀፍ ድርጅቶች በወቅታዊው የኦሮሚያ ክልል ተቃውሞ የተናጥል ምክክርን እያካሄዱ እንደሚገኝም ከሃገር ቤት የተገኘ መረጃ አመልክቷል።

የአክሰስ ሪል ስቴትና የዘመን ባንክ መስራች አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ታሰሩ

ኢሳት (ጥር 3 ፥ 2008) የአክሰስ ሪል ስቴት እንዲሁም የዘመን ባንክ መስራች አቶ ኤርሚያስ አመልጋ መታሰራቸውን ከአዲስ አበባ የደረስን ዜና አመለከተ። በመንግስት ዋስትና ወደሃገር ቤት ከተመለሱ ወራት ብቻ ያስቆጠሩት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ፣ ተመልሰው የታሰሩበት ዝርዝር ምክንያት ባይገለጽም፣ ከአክሰስ ሪል ስቴት ጋር የተያያዘ መሆኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል። ሃይላንድ ውሃን በማምረት ወደ ኢትዮጵያ ገበያ ውስጥ በመግባት በንግዱ አለም ታዋቂ የሆኑት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በየካቲት ወር 2005 ዓ ም ከመንግስት ጋር ባለመግባባት ከሃገር የወጡ ሲሆን፣ በመንግስት ተሰጣቸው በተባለ ዋስትና በየካቲት ወር 2007 ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል። ለሁለት ዓመታት ያክል በዱባይ ቆይተው ወደኢትዮጵያ የተመለሱት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ በነሃሴ ወር 2007 ከአክሰስ ቦርድ ሊቀመንበርነታቸው እንዲነሱ የተደረጉ ሲሆን፣ በርሳቸው ምትክ ወ/ሮ መብራት ወልደትንሳዔ የተባሉ ባለአክሲዮን መሾማቸው ታውቋል። በዋስትና ወደሃገር ቤት የተመለሱት አቶ ኤርሚያስ አመልጋ የተገባላቸውን በአደባባይ የተነገረው ቃል ታጥፎ ወደእስር ቤት የገቡበት ሁኔታ ግልጽ አልሆነም።
Ermias-Amelga

Tuesday, 5 January 2016

የአዳማ ዩንቨርስቲ ተማሪዎች በአጋዚ ወታደሮች ግድያ፣ ድብደባና ወከባ ደረሰባቸው

ኢሳት (ታህሳስ 26 ፥ 2008)

በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለውን የመሬት ዘረፋና የጅምላ ጭፍጨፋን  በመቃወም ላይ በነበሩ በአዳማ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ተቃውሞውን ለማስቆም በተሰማሩ የጸጥታ ሃይላት መካከል ግጭት እንደተፈጠረ የአይን እማኞች ከስፍራው አስታወቁ።ሰኞ ጠዋት የተጀመረው ይህ ተቃውሞ፣ ተማሪዎቹ በአዳማ ዩንቨርስቲ ውስጥ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ በኦሮሚያ ክልልና በሌላው የኢትዮጵያ ክልሎች ላይ እየደረሰ ያለው ጭፍጨፋና፣ ወከባና፣  እንግልትን እንዲቆም ሲጠይቁ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።አመጹን ለማስቆም ቀደም ብሎ በአካባቢው የሰፈረው ብዛት ያለው የአጋዚ ክፍለጦር እንደተሰማራ የተገለጸ ሲሆን፣ ተማሪዎችም ከመሬት ወረራና ከሰብዓዊ መብት ጥሰት በተጨማሪ የአጋዚን በትምህርት ማዕከል መስፈር በጽኑ ተቃውመዋል።ተቃውሞ እየተደረገ በነበረበት ወቅት የአጋዚ ክፍለጦር አባላት ተማሪዎች ላይ ጥይት እንደተኮሱና፣ ተማሪዎች ደግሞ ራሳቸውን ለመከላከል ይሯሯጡ እንደነበር የአይን እማኞች ገልጸዋል። የአጋዚ ወታደሮች አስለቃሽ ጋዝ በዩንቨርስቲ ግቢ እንደተጠቀሙ እነዚሁ የአይን እማኞች ለኢሳት ገልጸዋል።
በግጭቱም ወቅት አንድ ተማሪ እንደተገደለ ሲታወቅ፣ በጥይት የቆሰሉ ተማሪዎች ደግሞ በአምቡላን ወደሆስፒታል ተወስደዋል።  የአጋዚ ወታደሮች ብዛት ያላቸው ተማሪዎችን እየደበደቡ ጉድጓድ ውስጥ እንደወረወሯቸው የአይን እማኞች ለኢሳት አስረድተዋል።የፖሊስን ጥይት፣ አስለቃሽ ጋዝና፣ ዱላ ለማምለጥ ብዛት ያላቸው ተማሪዎች ከአዳማ ዩንቨርስቲ ጀርባ በሚገኘው ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ተጠልለው የነበረ ቢሆንም፣ የአጋዚ ሃይሎች ወደዚያ በመሄድ ተማሪዎችን እየደበደቡ እንዳስወጧቸው ታውቋል። በኋላም አብዛኞቹን ተማሪዎች ከቤተክርስቲያን አስወጥቶ በማሰለፍ ወደ ግቢ ይዘዋቸው ሄደዋል ተብሏል። የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪዎችም የፖሊስን ድርጊት ዝም ብሎ ከማየት ውጭ ምንም ነገር ማድረግ አለመቻላቸውን ለማወቅ ተችሏል።
ከዚህ በተጨማሪ የአጋዚ ክፍለጦር ወታደሮች የአውቶቡስ መነሐርያን በመዝጋት ተማሪዎች ወደቤተሰቦቻቸው እንዳይሄዱ እንዳደረጉ ታውቋል። አውቶቡስ ተራ የሚገባ ሰው መታወቂያ እያሳየ እንደነበርና፣ የዩንቨርስቲ ተማሪዎች ግን ወደግቢው እንዳይገቡ እንዳልተፈቀዳላቸው የአይን እማኞች ለኢሳት ተናግረዋል።ተማሪዎቹ ተቃውሟቸውን በሰላማዊ መንገድ የገለጹ ቢሆንም፣ የአጋዚ ወታደሮች ግን ያለርህራሄ ተማሪዎች እየደበደቡ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።የኦሮሚያ ፖሊስ በአካባቢው ቢኖርም፣ ተማሪዎችን ይደበድቡና ያዋክቡ የነበሩት ግን የታጠቁ እና ለውጊያ ዝግጁ የሆኑ የመደበኛ ሰራዊት አባላት እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል።
የማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ ግጭት ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የዩንቨርስቲ ግቢ በከባድ መሳሪያ ጭምር እየተጠበቀ እንደሆነ የአይን እማኞች ለኢሳት ገልጸዋል።ከማስተር ፕላን ጋር በተያያዘ በሃረማያ፣ አምቦ፣ ዲላ፣ እና በሁሉም በአገሪቱ ባሉት ሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለሁለት ወራት በተካሄደ ተቃውሞ፣  ከ125 በላይ የሚሆን የሰው የህይወትና ከፍተኛ ንብረት መውደሙ ይታወቃል። አሁንም በአብዛኛው የኦሮሚያ ክፍሎች ከፍተኛ ግጭቶት እየተከሰቱ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በኢትዮጵያ ያለው ርሃብ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አሳወቀ

ታኀሳስ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የዓለም የምግብ ድርጅት በኢትዮጵያ ያለው የድርቅ ሁኔታ እየከፋ መምጣቱንና ዜጎች አፋጣኝ እርዳታ ካልተደረገላቸው በአገሪቱ የሚደርሰው ሰብዓዊ ቀውስ እጅግ አደገኛ መሆኑን በሪፖርቱ ገልጿል።

በኢትዮጵያ በተከሰተው የአየር መዛባት ኤሊኖ ምክንያት ወቅቱን ጠብቆ ዝናብ ባለመዝነቡ በቂ ምርት መሰብሰብ ያልተቻለ ሲሆን እንስሳትም በድርቁ ሰበብ ሞተዋል።
ቁጥራቸው ከ10 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን አፋጣኝ የምግብ እርዳታ የሚያስፈልጋቸው ሲሆን የዓለም የምግብ ድርጅት 7.6 ሚሊዮን የሚሆኑትን በ2016 ዓ.ም ለመርዳት መዘጋጀቱንና ባለፉት ስድስት ወራቶች ውስጥ ከ5% ያነሰ የምግብ አቅርቦት ግብዓቶችን ማድረሱን የድርጅቱ ቃል አቀባይ እስቴፋን ጁሪክ አስታውቀዋል።
በኢትዮጵያ የተከሰተው ድርቅ ባለፉት ሰላሳ ዓመታት ተከስተው ከነበሩት ሁሉ የከፋውን ቀውስ ያስከተለ መሆኑን የተባባሩት መንግስታት ድርጅት በሪፖርቱ ማሳሰቡን ዩኤን ኒውስ ዘግቧል።
በተጨማሪም በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይና አማራ ክልል፣ በምስራቅ ኦሮሚያና ሶማሊያ ድርቁ ባስከተለው ችግር ሕጻናት በተመጣጠነ የምግብ እጥረት ምክንያት ለሞት መጋለጣቸውንና በአገሪቱ ያለው የርሃብ ተጠቂዎች ቁጥር 20 ሚሊዮን እንደሚጠጋ የካቶሊክ የእርዳታ ድርጅትን ጠቅሶ አልጀዚራ ዘግቧል። ከየአካባቢው በተሰባሰቡ መረጃዎች መሰረት በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እንዲሁም በትግራይ የዕርዳታ አሰጣጡ ስራ መቀነሱ፣ ተረጂዎች ባሉባቸው ወረዳዎችና ቀበሌዎች በቂ የዕርዳታ እህል እየቀረበ አለመሆኑ፣ የሚመጣውም ዕርዳታ ፍትሐዊ በሆነ መልኩ ለተረጂዎች እየተሰራጨ አለመሆኑ አሳሳቢ ሆኖአል፡፡

በኦሮምያ ዜጎች በህወሃት ንብረቶች ላይ የኢኮኖሚ ማእቀብ እየጣሉ ነው

ታኀሳስ ፳፮ (ሃያ ስድስት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-

በኦሮምያ ህዘባዊ ተቃውሞው እንደቀጠለ ሲሆን፣ ዜጎች በህወሃት ኩባንያዎች ላይ እርምጃ እየወሰዱ ነው። ትንናት በምስራቅ ሀረርጌ ቆቦ ከተማ የተጀመረው ተቃውሞ ወደ መሰላ ከተማም ተዛምቷል። የኢህአዴግ ወታደሮች በሚወስዱት ጭካኔ የተሞባለት እርምጃ እስካሁን 3 ሰዎች መገደላቸውን ከስፍራው የደረሰን ዜና ያመለክታል። የስርዓቱ ወታደሮች የሚወስዱት ጭካኔ የተሞላበት የሃይል እርምጃ ያሳሰባቸው የክልሉ ነዋሪዎች፣ የህወሃት ንብረት በሆነው ሰላም አውቶብስ ላለመሳፈር እንቅስቃሴ ጀምረዋል:፡ የክልሉ ወኪላችን እንዳለው ዜጎች በሰላም አውቶቡስ አንሳፈርም ማለታቸው ብቻ ሳይሆን፣ አውቶቡሱ በአካባቢው እንዳይንቀሳቀስ እየወሰዱት ያሉት እርምጃ ስጋት ላይ የጣለው ፣ ገዢው ፓርቲ፣ በእያንዳንዱ የሰላም ባስ ተሽከርካሪ ላይ ጠባቂ ወታደሮችን ለመመደብ ተገዷል።

ባለፉት 3 ቀናት በክልሉ የነበረው የሰላም አውቶቡስ እንቅስቃሴ የቀነሰ ሲሆን፣ ትናንት በአንዳንድ የኦሮምያ አካባቢዎች የተንቀሳቀሱ አውቶቡሶች በወታደሮች ታጅበው ታይተዋል። በኦሮምያ ክልል ውስጥ በሚሰሩ በሁሉም የሰላም አውቶቡሶች ውስጥ ጠባቂ ወታደሮች መመደባቸውን ዘጋቢያችን ገልጿል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአጋዚ ወታደሮች በክልሉ ህዝብ ላይ የወሰዱት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ መከፋፈል መፍጠሩን፣ አንዳንድ የኦሮሞ ተወላጅ የሰራዊቱ አባላት እየገለጹ ነው። ከፍተኛ መፈራራትና ቅሬታ አለ የሚሉት ምንጮች፣ የገዢው ፓርቲ ካድሬዎች “የተወሰደው እርምጃ ተገቢ ነው” ብለው ሌላውን ሰራዊት ለማረጋጋት እየተሯሯጡ ነው። ቅሬታው የእሰፋ በመምጣቱ በመሃል አገር ውስጥ የሚገኙ ወታደሮችና አዛዥ መኮንኖች እርስ በርስ እንዲጠባበቁ እንዳደረጋቸው አክለው ገልጸዋል።
ገዢው ፓርቲ በሚወስደው እርምጃ የተጎዱ በርካታ ዜጎች ፎቶግራፎች በማህበራዊ የመገናኛ ብዙሃን እየተሰራጩ ነው። እስካሁን ደድረስ ባለው መረጃ ከ100 በላይ ሰዎች በወታደሮች ተገድለዋል። በሺዎች የሚቆጠሩ ደግሞ ታስረዋል።

በኦሮሚያ ክልል ግድያው እና እስራቱ ቀጥሏል፥ ዴሞክራሲያዊ ሃይሎች እንዲተባበሩም ጥሪ ቀርቧል

ኢሳት (ታህሳስ 26 ፥ 2008)

የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ በበላይነት የሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት በአዲስ አበባ ዙሪያ ሊተገበር የተዘጋጀውን ማስተር ፕላን በመቃወም ሰላማዊ ተቃውሞ ያሰሙ ዜጎችን መግደሉን፣ መደብደቡንና፣ ማዋከቡን አጠናክሮ መቀጠሉ ታወቀ።በኦሮሚያ ስላለው ስለወቅታዊ ሁኔታ አጠቃላይ ሁኔታ ዝርዝር እንዲሰጡን የተጠየቁት ዶ/ር መረራ፣ በመንግስት ሃይሎች ዜጎችን የማሰሩ ሄደት አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ተናግረዋል። ባለፈው እሁድ በሃገረማሪያም ይኖር የነበረ አንድ የኦፌኮ አመራርና የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመንግስት ሃይሎች ተይዘው እንደታሰሩ ዶ/ር መረራ ለኢሳት ገልጸዋል።
የህወሃት/ኢህአዴግ መንግስት የተቃውሞው አስተባባሪዎች ናቸው ያላቸውን የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ አመራር አባላት አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ደጀኔ ቱፋ እና የወጣቶች ጉዳይ ሃላፊ የነበሩት አቶ ጉርሜሳ አየነውን ማሰሩን መዘገባችን ይታወሳል። በቅርቡም የአቶ በቀለ ነጋአ በቁም እስር እንዲሆኑ እንደተደረገ ታውቋል። አቶ በቀለ ነጋአ በቁም እስር ላይ እያሉ ለሚዲያ ምንም አይነት መረጃ እንዳይሰጡና ወደ ቢሮ ወይም ወደ ፈለጉበት አካባቢ መንቀሳቀስ እንዳይችሉ እገዳ እንደተጣለባቸው ለማወቅ ተችሏል።
እስካሁን ድረስ ከ4ሺ በላይ የሚሆኑ ዜጎች በማስተር ፕላን ሰበብ እንደታሰሩ ሲታወቅ፣ አሁንም በመላው ኦሮሚያ ተቃዋሚ ናቸው ተብለው የተጠረጠሩትን ሁሉ እየታደኑ መታሰራቸው ተገልጿል። የታሰሩት የአመራር አባላትም አብዛኞቹ እስካሁን ድረስ ከቤተሰቦቻቸው ጋር እንዳይገናኙ በጸጥታ ሃይሎች ተከልክለዋል።
የኦሮሞ ኮንግሬስ አባላት ከመታሰራቸው ውጪ ምንም አይነት መረጃ ከመንግስትም ሆነ ከሌሎች አካላት ማግኘት እንዳልቻሉ ዶ/ር መረራ ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ አስረድተዋል።
ዶ/ር መረራ “የኢትዮጵያ መንግስት የፖሊስ ወይም የህግ አካላት ያልሆኑ ከህግ ውጭ የሚንቀሳቀሱ ሃይሎች አሰማርቶ ባለበት ሁኔታ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግሬስ አቶ በቀለ ነጋአን ለራሳቸውና ለቤተሰቦቻቸው ደህንነት ሲል መጫን አይፈልግም” ብለዋል።
የደህንነት አካላት በአቶ በቀለ ነጋአ ቤተሰብ ላይ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ ማስፈራርያ እንደሰጧቸው መዘገባችን ይታወሳል። አቶ በቀለ ነገአ በራሳቸውና በቤተሰባቸው ላይ ወስነው መንቀሳቀስ ከፈለጉ መብታቸው እንደሆነም የደህንነት ሰዎች እንደነገሯቸው ለመገናኛ ብዙሃን ባሰራጩት ጹሁፍ አስታውቀው ነበር።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግሬስ አባላት ቢታሰሩም ፓርቲው ስራውን አጠናክሮ መስራቱን እንደቀጠለ ለኢሳት የገለጹት ዶር መረራ፣ “መንግስት የተወሰኑ አባሎቻችንን ቢያስርብንም፣ አሁን በዋናነት መልሶ የማደራጀት ስራ እየሰራን ነው”  ብለዋል።
በአዲስ አበባ እስካሁን ድረስ ለምን ሰላማዊ ሰልፍ እንዳላደረጉ ለተጠየቁት ጥያቄ ዶር መረራ ሲመለሱ፣ የኢትዮጵያ መንግስት ሲፈልግ ህግን፣ ካልፈለገ የራሱን ህግ የሚጠቀም  በመሆኑ ሰላማዊ ሰልፍ ከልክሎናል ብለዋል። በመሆኑም ኢህአዴግ “አታደርጉም የሚል ውሳኔ ሲሰጥ ህገመንግስትን እየጣሰ፣ እኛ ግን ህግ ያልሆነውን የራሱን ህግ እንድናከብር የሚፈልግ ፓርቲ ነው” ብለዋል።
ሆኖም ዶ/ር መረራ ኢህአዴግ ፈቀደ አልፈቀደ ህዝቡ በየክፍለሃገሩ ለሰላማዊ ሰልፍ እየወጣ እንደሆነ አብራርተዋል።  ትግሉ አዲስ አበባ ሲደርስ ሰላማዊ ህዝቡ ሰልፍ መውጣቱ አይቀሬ መሆኑን ለኢሳት በሰጡት ቃለምልልስ ገልጸዋል።
ዶር መረራ የኢትዮጵያ መንግስት የገባበት መንገድና ግትር አቋሙ እጅግ አደገኛ፣ ማንንም እንደማይጠቅም መሆኑን አስረድተው ወደ እርቅና ሰላም የሚያመጣ መንገድ መከተል እንደሚያስፈልግ መክረዋል። በመቀጠልም የኢትዮጵያ ህዝብ ለመብቱ በጋራ እንዲታገል ዶ/ር መረራ ጥሪ አቅርበዋል። የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሃይሎች ተሰባስበው ህዝቡን በመምራት ለሁላችን የምትሆን ዴሞክራቲክ ኢትዮጵያን ለመመስረት የሚያስችል አቅጣጫ መቀየስ እንዳለባቸው ጥሪ አስተላልፈዋል።
በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ተቃውሞ ተባብሶ መቀጠሉን መረጃዎች ያመለክታሉ። በትናንትናው ዕለት በአዳማ ላይ አንድ ሰው ተገሎ መገኘቱንና፣ ሰሜን ሸዋ አቦቴ አካባቢ ሌላ ሰው ተሰቅሎ እንደተገኘ ለኢሳት የደረሱ መረጃዎች ያለመክታሉ። በማስተር ፕላን ሰበብ የተነሳው ተቃውሞ በሌሎች የኦሮሚያ አካባቢዎች እንደገና አገርሽቷል። በምዕራብ ሸዋ በሃረር መስመር ጨለንቆ እና ቆቦ ላይ በትናንትናው ዕለት  የታሰሩት ይፈቱ የሚል ተቃውሞ እንደነበረም ለማወቅ ተችሏል።