Tuesday, 23 February 2016

በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ለመቆጣጠር ህወሃት/ኢህአዴግ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

በኦሮሚያ ክልል የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ ለመቆጣጠር ህወሃት/ኢህአዴግ የማያዳግም እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ
ኢሳት (የካቲት 15 ፥ 2008)
በኦሮሚያ ክልል ለሶስተኛ ወር ቀጥሎ ያለውን ተቃውሞ ለመቆጣጠር መንግስት እየወሰደ ያለውን እርምጃ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ማክሰኞ አስታወቀ። 
በጉዳዩ ዙሪያ መግለጫን የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ በክልሉ በበርካታ አካባቢዎች እየተካሄደ ካለው ተቃውሞ ጀርባ የጥፋት ሃይሎች ይገኛሉ ሲሉ ገልጸዋል። 
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የተደራጁ የጥፋት ሃይሎች ያሏቸውን አካላት በስም ባይጠቅሱም መንግስትን የማፈራረስና የመቀየር ተልዕኮ አላቸው ሲሉ ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ተናግረዋል። 
ድርጊቱንም ለመቆጣጠር መንግስት የማያዳግም እርምጃን እንደሚወስድ ገልጸው በምዕራብ አርሲና በሃረር አካባቢዎች ተቃውሞ መቀጠሉን አመልክተዋል።
የአሜሪካ መንግስትና የአውሮፓ ህብረት የመንግስት የጸጥታ ሃይሎች እየወሰዱ ያለውን የሃይል እርምጃ በማውገዝ የኢትዮጵያ መንግስት ከድርጊቱ እንዲቆጠብና ለተቃውሞ ሰላማዊ ምላሽን እንዲሰጥ ማሳሰባቸው የታወሳል።
በክልሉ እየተካሄደ ያለው ተቃውሞ ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ያለፉ የመብት ጥያቄን ያካተተ እንደሆነ የሚገልጹት እነዚሁ አካላት በሰላማዊ ሰዎች ላይ የተፈጸመ ግድያን ማጣራት እንዲካሄድበት ጠይቀዋል።
በዚሁ ጉዳይ ዙሪያ ሰኞ መግለጫን ያወጣው ሂውማን ራይትስ ዎች በበኩሉ ሶስተኛ ወሩን በያዘው ተቃውሞ ከ200 በላይ ሰዎች መገደላቸውንና እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠሉን አመልክቷል።
የአለም አቀፉ ማህበረሰብ በኦሮሚያ ክልል ቀጥሎ ያለው ተቃውሞ መፍትሄን እንዲያገኝ በመጠየቅ ላይ ቢሆኑም መንግስት የጥፋት ሃይሎች እጅ አለበት በማለት የሚወስደውን የሃይል እርምጃ እንደሚቀጥል ማክሰኞ ገልጿል።

Sunday, 21 February 2016

የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አዛዦች በአዲስ አበባ ስብሰባ አካሄዱ፡፡ ስብሰባው ያለምንም ውጤት በግጭት ተቋጭቷል


የፌደራል ፖሊስ ከፍተኛ አዛዦች በአዲስ አበባ ከየካቲት 9 እስከ 12 2008 ዓ.ም የተሰበሰቡ ሲሆን የመልካም አስተዳደር ችግር፣ የፀጥታ ሁኔታ እና የአባላት መክዳት እያነሱ ከተወያዩባቸው አጀንዳዎች መካከል ዋነኞቹ ናቸው፡፡ በስብሰባው ላይ የአማራና የኦሮሞ ተወላጅ አዛዦች "እኛ ከእናንተ የተሻለ የትምህርት ደረጃና ልምድ እያለን ሁሉንም ቦታ ጠቅልላችሁ ይዛችሁት ተገቢው ቦታ አልተሰጠንም..." በማለት ህወሓቶችን ልካቸውን ነግረዋቸዋል፡፡
ህወሓቶች በፌደራል ፖሊስ ተቋም ውስጥ ባሰፈኑት ዘረኝነት ምክንያት ሰራዊቱ በመፍረስ ላይ እንደሚገኝ ስብሰባው ላይ በተደጋጋሚ ...ተወስቷል፡፡ በውይይቱ ላይ ተቃውሟቸውን ያሰሙ የኦሮሞና አማራ ተወላጅ አመራሮች ከህወሓቶች "የእናስራችኋል" ማስፈራሪያ ደርሷቸዋል፡፡
በመጨረሻም ስብሰባው ወደ ለየለት ንትርክና አምባጓሮ በማምራቱ አብዛኞቹ አዛዦች እንዲበተኑ ተደርገው ውይይቱ በጥቂት ዋና፣ ዋና አመራሮች ለተጨማሪ ጊዜ ተካሂዷል፡፡ የፌደራል ፖሊስ አደረጃጀት ሊፈርስ እንደሚችልም ጭምር ጭምጭምታ ተሰምቷል፡፡
በተያያዘ ዜና የሚከዱ የፌደራል ፖሊስ አባላት ቁጥር አሁንም ከቀን ወደ ቀን እየናረ መምጣቱ እየተነገረ ነው፡፡ በጎንደር ብቻ ቢያንስ በቀን 3 የፌደራል ፖሊስ አባላት እንደሚከዱ የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ ዜና ምንጮች ገልፀዋል፡፡
 #የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ#

የ24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በገፍ እየገዱ መሆናቸው ታወቀ

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
የ24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በገፍ እየገዱ መሆናቸው ታወቀ፡፡
በሰሜን ምዕራብ የኢትዮጵያ ክፍል በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ የነፃነት ድርጅቶች ለረጅም ዓመታት የዘለቀ የሽምቅ ውጊያ ጥቃት ሲደርስበት፣ እስከ ሬጅመንት ድረስ እየተደመሰሰ ሲፈርስና እንደገና በሰው ኃይልና በጦር መሳሪያ በተደጋጋሚ ሲገነባ የኖረው 24ኛ ክፍለ ጦር አባላት በውጊያ በእጅጉ ተሰላችተውና በስርዓቱ ተስፋ ቆርጠው በከፍተኛ ሁኔታ በመክዳት ላይ ናቸው፡፡
በተለይም ደግሞ የሽምቅ ውጊያ ጥቃቶች የመጀመሪያ ገፈት ቀማሽ የሆኑ በሁመራና አካባቢው ሰፍረው የቆዩ ሬጅመንቶች ውልቃቸውን በመቅረታቸው ከአዘዞ እና ጭልጋ ሌሎች ሬጅመንቶችን አንስቶ የመተካት እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡
የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ የነፃነት ድርጅቶች ክንድ እየፈረጠመ መምጣት እና ዕለት ከዕለት በሚያደርጓቸው የሽምቅ ውጊያ ጥቃቶች የሚያሳርፉት ዱላ እየበረታ መሄድ በዋነኝነት አርበኝነት በሚፋፋምበት አካባቢ የሚገኘውን 24ኛ ክፍለ ጦር አፍረክርኮታል፡፡

Friday, 19 February 2016

እነ በቀለ ገርባና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ለመጋቢት 9 ተቀጠሩ

እነ በቀለ ገርባና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ለመጋቢት 9 ተቀጠሩ
*ጋዜጠኛ ጌታቸው ጨለማ ቤት ታስሯል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብር ተጠርጥረው በፌደራል ፖሊስ ወንጀል ምርመራ ማዕከል በእስር ላይ የሚገኙት የኦፌኮ አመራሮች እነ በቀለ ገርባ እና ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው የ28 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ዛሬ የካቲት 11/2008 ዓ.ም አራዳ ፍርድ ቤት የቀረቡት የኦፌኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ በቀለ ገርባ እና በተመሳሳይ ወንጀል ተጠርጥረው የታሰሩ ሌሎች የፓርቲው አባላት፣ እንዲሁም ታህሳስ 15/2008 ዓ.ም ለእስር የተዳረገው የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው እና የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው አቶ ዳንኤል ተስፋየ ፖሊስ ምርመራየን አልጨረስኩም በሚል የጠየቀባቸው የ28 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ተፈቅዶለታል፡፡...
የጋዜጠኛ ጌታቸው ሺፈራው ጠበቃ አቶ አምሃ መኮንን ከችሎቱ በኋላ እንደገለጹት ፖሊስ ‹‹ግብረ አበር መያዝ ይቀረኛል፣ ምስክር አላደራጀሁም…›› የሚል ካለፈው ጋር ተመሳሳይ ምክንያት በመስጠት ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ ጠይቋል፡፡ ደንበኛቸው ከታሰረ ጀምሮ አንድም ቀን አግኝተው ለማነጋገር እንዳልተፈቀደላቸው ለችሎት የገለጹት ጠበቃ አምሃ፣ ጌታቸው ጠበቃውን ሳያነጋግር ቃሉን ለፖሊስ ለመስጠት ፍቃደኛ እንዳልሆነ ፍርድ ቤቱ እንዲገነዘብላቸው በድጋሜ ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡
ጋዜጠኛ ጌታቸው በበኩሉ ያለፉትን 28 የምርመራ ቀናት የተጠየቀው ነገር እንደሌለ፣ ነገር ግን በጨለማ ቤት እንዳሰሩት ለችሎት ገልጹዋል፡፡
በተመሳሳይ የምርመራ መዝገብ የሚገኙት አቶ ዳንኤል ተስፋየ እና አቶ ሸዋታጠቅ ኃ/መስቀል በበኩላቸው ቤተሰቦቻቸው እንዲጠይቋቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል፡፡
በተመሳሳይ ችሎት የቀረቡት እነ በቀለ ገርባም እንዲሁ ፖሊስ ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ጠይቆባቸው 28 ቀናት ተፈቅዶለታል፡፡ የዛሬውን የችሎት ውሎ ለመከታተል የተጠርጣሪዎች ቤተሰቦችና ወዳጆቻቸው ፍርድ ቤት ግቢ ቢገኙም ችሎቱ ዝግ በመደረጉ አንድም ሰው መከታተል እንዳልቻለ ታውቋል፡፡


Sunday, 14 February 2016

በጎንደር ከተማ የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ አባላት በገፍ እየከዱ ነው

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
‪#‎በጎንደር‬ ከተማ የሚገኙ የፌደራል ፖሊስ አባላት በገፍ እየከዱ ነው፡፡
በጎንደር ከተማና አካባቢው የጦር ካምፕ መስርተውም ሆነ ከቦታ ቦታ እየተንቀሳቀሱ አገዛዙን ሲያገለግሉ የቆዩ የፌደራል ፖሊስ አባላት በከፍተኛ ሁኔታ ከነትጥቃቸው በመሰወር ላይ ናቸው፡፡ ባለፈው ሳምንት ውስጥ ብቻ ከ30 በላይ ፌደራል ፖሊሶች ከነትጥቃቸው ስርዓቱን በመቃወም ከየካምፓቸውና በውሎ ጠፍተዋል፡፡
የህወሓት አገዛዝ ይህን የፌደራል ፖሊስ አባላት መክዳት ለማስቆም ተደርጎ የማይታወቀውን ጥቅማጥቅምና የማዕረግ እድገት ለመስጠት ቢወስንም ሰራዊቱ እንደበፊቱ በቀላሉ ተሸውዶ ሰጥ ለጥ ብሎ ወደ ሎሌነት ተግባሩ ሊመለስ አልቻለም፡፡ እንዴውም በተቃራኒው የሚጠፉ የፌ...ደራል ፖሊስ አባላት ቁጥር ከቀደመው ጊዜ ጋር ሲነፃፀር አየናረ መጥቷል፡፡
በመሆኑም ለዛሬ ሰፊ ስብሰባ ሊደረግ ፕሮግራም ተይዟል፡፡


Saturday, 13 February 2016

በጎንደር ከተማ ጎሃ ሆቴል ውስጥ ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ በተካሄደው ስብሰባ

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የአማራ ክልል ሹሞች በጎንደር ጎሃ ሄቴል ለሦስት ተከታታይ ቀናት ያደረጉት ድብቅ ስብሰባ ያለምንም ውጤት በፀብ ብቻ ተቋጨ፡፡ በህወሓቶችና በብአዴኖች መካከል የተካረረ ፍጥጫና ንትርክ ተከስቶ የነበረ መሆኑም ተደርሶበታል፡፡
===================================================
በጎንደር ከተማ ጎሃ ሆቴል ውስጥ ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የተገኙት የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናት አባይ ፀሐዬ፣ ስብሃት ነጋ፣ ደብረ ፂዮን ገ/ሚካኤል፣ አባይ ወልዱ እና የትግራይ ክልል አስተዳደርና ፀጥታ ሹም ናቸው፡፡
ገዱ አንዳርጋቸው፣ አለምነው መኮንን እና መኳንንት /የአማራ ክልል ፀጥታ ሹም/ ደግሞ ከብአዴን ወገን የተገኙ የአማራ ክልል ሹማምንቶች ነበሩ፡፡
የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የህወሓት ዲቃላ የሆነው ብአዴን ባለስልጣናት በጎንደር ጎሃ ሆቴል ተሰብስበው የተነታረኩባቸው አጀንዳዎች ሁለት ሲሆኑ የወልቃይትን የአማራ ማንነት ጥያቄ እና ብረት ያነሱ የነፃነት ድርጅቶችን /በተለይም አርበኞች ግንቦት 7ን/ በሚመለከት ነው፡፡
የትጥቅ ትግል እያደረጉ የሚገኙ የነፃነት ድርጅቶችን በሚመለከት ህወሓቶች "ሰተት ብለው ከበረሃ ወደ ህዝቡ እንዲገቡ እያደረጋችኋቸው ነው..." በማለት ብአዴኖችን ወቅሰዋቸዋል፡፡
ከወልቃይት ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ደግሞ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪና የህወሓት ሊቀ መንበር የሆነው አባይ ወልዱ እንዲህ ብሏል፡፡
"ወልቃይት የትግራይ ነው! የአማራነት ጥያቄው በዚህ የማያቆምና ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን...!"
ቀጥሎም አባይ ወልዱ የአማራ ክልልን አስተዳዳሪ ገዱ አንዳርጋቸውን
"አንተ የአማራን ህዝብ የጦር መሳሪያ ያስታጠከው ሆነ ብለህ በትግራይ ላይ ጦርነት ለማወጅ ነው..." በማለት ተናግሮታል፡፡
ገዱ አንዳርጋቸውም በበኩሉ
"እኔ ህዝቡ በሀብቱ ገዝቶ ከጥንት ጀምሮ ታጥቆት የቆየውን ጦር መሳሪያ ህጋዊ ፈቃድ በመስጠት አፀናሁለት እንጂ ልክ እንዳንተ ከመንግስት ግምጃ ቤት አውጥቼ በገፍ አላስታጠቁትም፡፡ በትግራይ ህዝብ ላይ ጦርነት አወጅክ ላልከኝም የትግራይን ህዝብ ሰብስበህ በወልቃይት ህዝብ ላይ እርምጃ እንወስዳለን ብለህ በይፋ ጦርነት ያወጅከው አንተ ነህ፡፡" በማለት ለአባይ ወልዱ መልስ ሰጥቶታል፡፡
የጦር መሳሪያን በሚመለከት ደብረ ፂዮን ገ/ሚካኤል ገዱ አንዳርጋቸው የአማራን ህዝብ እንዳስታጠቀ ወቀሳ ሰንዝሯል፡፡ ደብረ ፂዮን ስለ ወልቃይት ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ የሚከተለውን በማለት ቁልጭ ያለ አቋሙን አስቀምጧል፡፡
"የወልቃይት ጉዳይ ክልል አንድን እንጂ ማንንም አይመለከተውም፤ ውሳኔውም ሊሆን የሚችለው የክልል አንድ ብቻና ብቻ ነው፡፡"
ለዚህ የደብረ ፂዮን ንግግር ገዱ አንዳርጋቸው ሲመልስ
"እኛ ሄደን ኑ አንላቸውም፤ ከመጡ ግን የማንቀበልበት ምንም ምክንያት የለም፤ ደግሞም ውሳኔ ማስቀመጥ ያለበት ራሱ የወልቃይት ህዝብ ነው፡፡"
በመሆኑም በሁለቱ ክልሎች /በትግራይና አማራ/ አስተዳዳሪዎች ማለትም በአባይ ወልዱና ገዱ አንዳርጋቸው መካከል ስብሰባው ውስጥ የተካረረ ፍጥጫ ተከስቶ ነበር፡፡
ህወሓቶች ለገዱ አንዳርጋቸው ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጥተውታል፡፡
በአጠቃላይ በጎንደር ጎሃ ሆቴል ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ የተካሄደው የህወሓቶችና የብአዴኖች ውይይት ያለምንም መግባባት በፀብ ብቻ ተጠናቋል፡፡

Thursday, 11 February 2016

ኦሮሚያ የመላው ኢትዮጵያዊ መላው ኢትዮጵያም የሁሉም ኦሮሞ ናት!

ኦሮሚያ የመላው ኢትዮጵያዊ መላው ኢትዮጵያም የሁሉም ኦሮሞ ናት!
ከጃዋር ሃሳብ የማልስማማበት እና የምስማማበትን ስለመለየት፤
የኛ ሀገር ፖለቲካ የቡዳ ፖለቲካ ነው እንዳሉት ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና አሁንም ድጋሚ ፖለቲካችንን ቡዳ ሊበላው ነው መሰል ጣት መቀሳሰር እና እነ እንትና እነ እንትና መባባል ልንጀምር ይመስላል… ምናባቱ እንግዲህ ካልደፈረሰ አይጠራም…
ጃዋር ሰሞኑን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በዋሽንግተን ዲሲ ካደረጉት ንግግር በኋላ በአራት ጉድዮች ላይ አስተያየት ሰጥቷል። ካነሳቸው ሃሳቦች ውስጥ በተወሰነ ደረጃ የምስማማባቸው ሃሳቦች ቢኖሩኝም በርካታ የማልስማማባቸው ሃሳቦችም አሉ። ከሁሉ ከሁሉ ግን በትልቁ የማልስማማበት፤ ኦሮሞ በሙሉ ተመሳሳይ ነው ብሎ ሁሉንም ኦሮሞዎች በአንድ ቅርጫት ውስጥ ለማስቀመጥ የሚሞክረው ነገር ሁልጊዜም በጣም የሚያበሳጨኝ ነው። (እነደሱ አባባል እርሱ በሚለው የማይስማማ ኦሮሞ ኦሮሞ አይደለም (ሲያናድድ!))
እኛ ኦሮሞዎች ሰዎች ነን። ምንም እንኳ የሰው ልጆች በሙሉ በፍጥረታቸው አንድ ናቸው ቢባልም፤ በአስተሳሰብ እና በአመለካከት ግን አንድ አይነት መሆን አይችሉም። ሁሉም ሰው የየራሱ አመለካከት እንዳለው ሁሉ፤ ኦሮሞዎችም የየራሳችን አመለካከት አለን። እኛ በፋብሪካ የተመረትን ሮቦቶች አይደለንም። የተለያየ አመለካከት የተለያየ አስተሳሰብ፣ የተለያየ የምፍትሄ አቅጣጫ፣ የተለያየ ምኞት እና ፍላጎት ያለን ሰዎች ነን። ይሄ ሰው በመሆናችን የተሰጠንም ጸጋ ነው። ጃዋር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፤ ‘’ከለዘብተኛ ኦሮሞዎች ጋር አብረን እየሰራን ነው’’ ማለቱን ተከትሎ በኦሮሞ ውስጥ ለዘብተኛ አክራሪ የለም ብሎ ይሞግተናል። ሞልቶ! በሁሉም ማህበረሰብ ውስጥ በአንድ ጉዳይ ላይ አክራሪ እና ለዘብተኛ እንዳለው ሁሉ በኦሮሞ ማህበረሰብ ውስጥም ይሄ አለ። ወደፊትም ይኖራል።
ለምሳሌ ያክልም፤ ራሱ ከጃዋር እና የመሳሰሉት ኦሮሚያ የኦሮሞ ናት ሲሉን እየሰማን ነው። በነገራችን ላይ የ ‘የ’ እና የ ’ለ’ ነገር በትርጉሙ ላይ ምንም የሚያመጣው ለውጥ የለም። ኦሮሚያ ለኦሮሞ ናት ተባለም ኦሮሚያ የኦሮሞ ናት ተባለም ምንም የፍቺ ልዩነት የላቸውም። (ወዳጃችን ጃዋር ኦሮሚያ ለኦሮሞ ናት አላልኩም ኦሮሚያ የኦሮሞ ናት ነው ያልኩት ሲል አይቼ ባውጠነጥን ባውጠነጥን ምንም ልዩነት አላየሁበትም።) የሆነው ሆኖ ጃዋር እንደሚያስበው ይሄ አስተሳሰብ የሁሉም ኦሮሞዎች አስተሳሰብ ነው። በኦሮሚያ የተነሳው ተቃውሞም ዋና ሃሳብ ይሄ ነው ይለናል።
እኛ ጃዋር ኦሮሞ አይደለም ብለን አንከራከርም። ነገር ግን እርሱ ብቻ ሳይሆን እኛም ኦሮሞዎች ነን። እንደኛ አስተሳሰብ ኦሮሚያ የመላው ኢትዮጵያዊ መላው ኢትዮጵያም የኦሮሞ ናት። እንኳንስ ኦሮሚያ እና ብሪታኒያ እና አሜሪካንን የመሳሰሉት ሀገሮች እንኳን የብርትሾች እና የአሜሪካኖች አይደሉም፤ የሁላችንም ናቸው እንጂ! (ምንም እንኳ እንደ ዶናልድ ትራምፕ አይነት ቀውሶች ይሄ አሳብ ቅዠት ቢመስላቸውም አሁን አለም ባለችበት ደረጃ ግን ማንም ሰው የሀገሪቱን ህግ እና ደንብ አክብሮ እስከኖረ ድረስ ሁሉም ሀገር የሁሉም ነው። በዛ መሰረት ነው ጃዋርም ሆነ እኔ በአሜሪካ እና እንግሊዝ የምንኖረው!)
በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ተቃውሞ ዋና ማጠንጠኛ ኦሮሞ ዘመዶቻችን አንድም በገዛ ወገኖቻቸው፤ (በኦህዴድ አባላት) አንድም ከፌደራል በሚሄዱት እነ አባይ ጸሃዬ የሚደርስባቸው ስር የሰደደ በደል ሞልቶ ስለፈሰሰ ነው፤ እንጂ ኦሮሚያ ለኦሮሞ ትሁን በሚል አይደለም። እንደዚ የሚሉ ቢኖሩም እንኳ በኔ አስተሳሰብ ስህተት ውስጥ እየገቡ ነው። ማንም ሰው በአግባቡ እና በደንቡ መሰረት እስከተንቀሳቀሰ ድረስ (በእግር ኳስ ቋንቋ ፌር ፕሌይ እስከተጫወተ) ሁሉም ሃገር የርሱ ነው። ኦሮሚያን ጨምሮ። ብቻ ገበሬዎችን ያለአግባብ አያፈናቅል። ብቻ ገበሬውን በገዛ መሬቱ ላይ ከአምራችነት ወደ ዘበኛነት አይቀይር እንጂ!
አሁን ኢህአዴግ እየፈጸመ ያለው ዘረፋ በኦሮሚያ ላይ ነውር ነው! በትግራይም ላይ ሲፈጸም ብልግና ነው! በአማራ ክልልም ሲደረግ ጸያፍ ነው።
ይልቅስ ጃዋር በብሄር ስለመደራጀት ያነሳው ነገር ላይ እስማማለሁ። ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ይሄ የኔ አመለካከት ነው ብለው በነገሩን መሰረት የብሄር ወይም ዘውጌ ፖለቲካዊ ስብስብ አይመስጣቸውም ብቻ ሳይሆን አፍራሽ ነው ሲሉም ኮንነውታል። በርግጥ ‘’እባብን ያየ በልጥ ይደነግጣል’’ እንዲሉ አሁን አሁን እየሆነ እንዳለው ነገር የብሄር አደረጃጀቶች የሚያስፈራ ነገር አላቸው። ቢሆንም ግን አፍራሽ ናቸው ብሎ ድምዳሜ ላይ መድረስ ከባድ ነው። ሰዎች በመሰላቸው መልኩ የመደራቸት እና የመታገል መብታቸው በጽኑ ሊከበር ይገባል። በሰለጠኑት ሃገራት በብሄር የተደራጁ ፓርቲዎች ለዴሞክራሲ ግንባታ አፍራሽ ሚና ሲጫወቱ አላየንም። እንደ ምሳሌም ስኮቲሽ ናሽናል ፓርቲ በ ዩናይትድ ኪንግደም ፖለቲካ ውስጥ ያለውን ተሳትፎ ማየት ይቻላል። እኛም ሃገር ቢሆን ፖለቲካችን አፍራሽ ሚና የሚኖረው ከአያያዛችን እንጂ ከአደረጃጀታችን አይመስለኝም። (እንደውም ከቤተሰብ ጉባኤ አንስቶ ብብሄር መደራጀት ተፈጥሯዊ ነው ብዬ አስባለሁ.... አፍራሽ የሚሆነው ክኔ ብሄር በላይ ላሳር ማለት ሲጀመር ነው! እሱን የሚገራ ሀገር አቀፍ ህግ መኖር ይኖርበታል!)
በኢሳት ቴሌቪዥን የኦሮምኛ ቋንቋ ዝግጅቶች መጀመራቸውን አስመልክቶ የኦሮሞን ህዝብ ትግል ለማዳከም ነው የሚለን ጃዋር ከላይ እንዳነሳሁት በኢሳት ቴሌቪዥን ላይ በአዘጋጅነት የሚሰሩትን ኦሮሞዎች ስለ ኦሮሞ ጉዳይ የማያስቡ ራሱን ደግሞ ከማንም በላይ ለኦሮሞ አሳቢ የማድረግ አዝማሚያ ነው ያየሁበት... ይሄኔ ይቺ ሰውዬ ቀስ ብላ እኔንም ለኦሮሞ አታስብም ትለኝ ይሆናል እኮ ብዬ ስቄ ትቼዋለሁ!
እያልኩ ልጻፍ ልተወው… በማለት እያሰብኩ ነው….
(ጋዜጠኛ አበበ ቶላ ፈይሳ አቤ ቶኪቻው)

Friday, 5 February 2016

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የምስክርነት ቃሉን ሰጠ

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የምስክርነት ቃሉን ሰጠ
*‹‹የህሊና እስረኛ ነኝ›› እስክንድር ነጋ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ 18 አመት እስር ተፈርዶበት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የመከላከያ ምስክርነት ቃሉን ሰጥቷል፡፡ 
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ ለሆነው አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ መከላከያ ምስክር ሆኖ ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ከእስር ቤት የቀረበው ጋዜጠኛ እስክንድር ዛሬ ጥር 27/2008 ዓ.ም ምስክርነቱን ሊያሰማ ችሏል፡፡ 
*‹‹የህሊና እስረኛ ነኝ›› እስክንድር ነጋ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በሽብርተኝነት ወንጀል ጥፋተኛ ተብሎ 18 አመት እስር ተፈርዶበት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የመከላከያ ምስክርነት ቃሉን ሰጥቷል፡፡ 
በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ አንደኛ ተከሳሽ ለሆነው አቶ ዘላለም ወርቃገኘሁ መከላከያ ምስክር ሆኖ ልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ከእስር ቤት የቀረበው ጋዜጠኛ እስክንድር ዛሬ ጥር 27/2008 ዓ.ም ምስክርነቱን ሊያሰማ ችሏል፡፡ 
ያለጠበቃ በግሉ የሚከራከረው ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ጋዜጠኛ እስክንድር እንዲያስረዳለት የሚፈልገው ጭብጥ ጡመራ ምንድነው፣ ከወንጀል ጋርስ ግንኙነት አለው ወይ፣ እና ሰብዓዊ መብት እና ዴሞክራሲ ላይ ስልጠና ስለሚሰጡ ድርጅቶችና የስልጠናው ይዘትን በተመለከተ እንደሆነ ቢያስታውቅም በጭብጡ ላይ አቃቤ ህግ ተቃውሞውን አሰምቷል፡፡ በዚህም አቃቤ ህግ ጡመራ ምንድነው፣ ወንጀልስ ነው ወይ የሚለው በምስክር ሳይሆን በህግ ድንጋጌዎች የሚረጋገጥ እንደሆነ በመግለጽ ተቃውሟል፡፡ ፍርድ ቤቱም ግራ ቀኙን ከሰማ በኋላ ጡመራ ወንጀል ስለመሆን አለመሆኑ የተያዘውን ጭብጥ ውድቅ በማድረግ ስለ ስልጠናውና አሰልጣኝ ተቋማት የተመዘገበው ጭብጥ ላይ ምስክሩ እንዲመሰክሩ ብይን ሰጥቷል፡፡
ብይኑን ተከትሎ ምስክሩ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ችሎት ፊት የቀረበ ሲሆን በመጀመሪያ በፍርድ ቤቱ የቀረቡለትን ጥያቄዎች መልሷል፡፡ ምስክሩ ሙሉ ስሙን፣ እድሜውን፣ ስራውንና ለምን እንደመጣ፣ እንዲሁም ከተከሳሾች ጋር ስለመተዋወቁ ለቀረቡለት ጥያቄዎች መልስ ሰጥቷል፡፡ እስክንድር ‹‹ስራ›› ተብሎ ሲጠየቅ፣ ‹‹ጋዜጠኛ ነበርኩ›› ብሏል፡፡ ‹‹አሁንስ›› የሚል ጥያቄ ፍርድ ቤቱ አቅርቦለት፣ ‹‹አሁን የህሊና እስረኛ ነኝ›› ሲል መልሷል፡፡
ተከሳሹ ዘላለም ወርቃገኘሁ በዋና ጥያቄ ተከሳሹ ውጭ ሀገር ሊወስደው ነበር ተብሎ በክሱ ላይ ስለተጠቀሰው ስልጠና ምስክሩ እንዲያብራሩለት ጠይቋል፡፡ ምስክሩም ‹‹ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማት ኢትዮጵያን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሀገራትንም የሚያሳትፍ ስልጠና በሰብዓዊ መብት፣ በሚዲያ ‹ኢቲክስ›፣ እና በዴሞክራሲ ላይ ይሰጣሉ፡፡ ድርጅቶቹ የተለያዩ ቢሆንም በሰብዓዊ መብት ጉዳይ ላይ መርሃቸው ተመሳሳይና ዓለም አቀፍ ነው›› በማለት መስክሯል፡፡
ድርጅቶቹን በስም መጥቀስና የሚገኙበትንም ሀገር ለፍርድ ቤቱ መግልጽ ይቻል እንደሆነ ምስክሩ ተጠይቆ ‹‹የተቋማቱ መገኛ ምዕራቡ ዓለም ነው፡፡ በዴሞክራሲ የዳበሩ ሀገራት ነው ዋና መቀመጫቸው፡፡ ሲ.ፒጄ፣ ፍሪደም ሀውስ፣ አምንስቲ ኢንተርናሽናል እና አርቲክል 19 የመሳሰሉትንም በስም መጥቀስ ይቻላል፡፡ እኔም ከነዚህ ተቋምት ውስጥ በአንዱ የተሰጠ ስልጠና አዲስ አበባ ላይ ተካፍየ ነበር፡፡ ስልጠናው ስለ ሰብዓዊ መብት፣ ስለ ሚዲያ፣ ስለ ዴሞክራሲ የሚያስተምር ነው፡፡ ስልጠናው ከሽብር ጋር ምንም ግንኙነት የለውም፤ ይህ እንደማስረጃ መቅረቡ ኢትዮጵያን ትዝብት ውስጥ የሚከትና የሚያሳዝን ነው›› ሲል ምስክርነቱን ሰጥቷል፡፡
ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ መቼ እንደታሰረ በመስቀለኛ ጥያቄ ተጠይቆ ‹‹መስከረም 2004 የሀሰት ክስ ቀርቦብኝ፣ በግፍ ተፈርዶብኝ ታስሬ እገኛለሁ›› ሲል መልሷል፡፡ እስክንድር ነጋ ጥቁር ሱፍ በደብዛዛ ሸሚዝ ለብሶ፣ ሙሉ ጥቁር መነጸር አድርጎና ነጠላ ጫማ ተጫምቶ ችሎት ፊት ቀርቧል፡፡
አንደኛ ተከሳሽ ዘላለም ወርቃገኘሁ ምስክሩ ምስክርነቱን ማጠቃለሉን ተከትሎ በመከላከያ ምስክርነት እንዲቀርቡለት የጠራቸው ሌላኛው ምስክር አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በተደጋጋሚ እንዲቀርቡለት ትዕዛዝ እንዲሰጥለት የጠየቀ ቢሆንም እስካሁን አለመቅረባቸው መንግስት ግለሰቡን ለማቅረብ ፍላጎት እንደሌለው ያሳያል ሲል ቅሬታውን አሰምቷል፡፡ ‹‹አሁን የተረዳሁት ነገር ከሳሼ የሆነው መንግስት አቶ አንዳርጋቸውን ከሚያቀርብ እኔን በነጻ መልቀቅ እንደሚቀለው ነው›› ብሏል ተከሳሹ፡፡
ተከሳሹ ከአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጋር በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች እንደተገናኜ አቃቤ ህግ መጥቀሱን በማስታወስ ምስክሩ መቅረባቸው ያለውን ተገቢነት አስረድቷል፡፡ ‹‹ምስክሩ እንዲቀርቡልኝ እፈልጋለሁ፡፡ ይህ የማይሆን ከሆነ ግን ፍርድ ቤቱ ከምስክሩ ጋር በተገናኘ ያለውን የክሱ ፍሬ ነገር አውጥቶ በቀሪው ላይ ብይን ይስጥልኝ›› ብሏል ተከሳሹ አቶ ዘላለም፡፡
ፍርድ ቤቱም ምስክሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲቀርቡ ትዕዛዝ በመስጠት ምስክርነታቸውን ለመስማት በሚል ለየካቲት 16/2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Thursday, 4 February 2016

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በፍርድ ቤት እየተጉላሉ መሆኑን አቤቱታ አሰማ

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በፍርድ ቤት እየተጉላሉ መሆኑን አቤቱታ አሰማ
*ተከሳሾች ችሎቱ እንዲቀየርላቸው ጠይቀዋል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
በፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14ኛ ወንጀል ችሎት እየታየ የሚገኙት እነ ብርሃኑ ተክለያሬድ በፍርድ ቤት እየተጉላሉ መሆናቸውን በመግለጽ ችሎት እንዲቀየርላቸው አቤቱታ አቅርበዋል፡፡
ዛሬ ጥር 26/2008 ዓ.ም ልደታ ፍርድ ቤት የቀረቡት ተከሳሾች አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ ወ/ት እየሩሳሌም ተስፋው፣ አቶ ፍቅረማርያም አስማማው እና አቶ ደሴ ካህሳይ ጉዳያቸውን እያየ የሚገኘው 14ኛ ወንጀል ችሎት ጉዳያቸውን በማጓተት እያጉላላቸው እንደሆነ በአቤቱታቸው ገልጸዋል፡፡ መዝገቡ ለዛሬ ተቀጥሮ የነበረው ለብይን ቢሆንም ተከሳሾች 14ኛ ወንጀል ችሎት እንዲቀየርላቸው አቤቱታ በማሰማታቸው ብይኑ ሳይሰማ ቀርቷል፡፡
1ኛ ተከሳሽ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ‹‹አቃቤ ህግ አንድ ምስክሩን ያሰማው ነሐሴ 12/2007 ዓ.ም ነው፡፡ የአንድ ምስክር ቃል በጽሁፍ ተገልብጦና ተመርምሮ ብይን ለመስራት ይህን ያህል ጊዜ መውሰድ አልነበረበትም፡፡ ለዚህ ሁሉ መጉላላት ይህ ችሎት አስተዋጽኦ አለው ብለን ስለምናምን ችሎቱ እንዲቀየርልን ለፍርድ ቤቱ ፕሬዚዳንት ቢሮ አቤት ብለናል፡፡ ስለዚህ ብይኑ ዛሬ ሊሰማብን አይገባም›› ብሏል፡፡
3ኛ ተከሳሽ ፍቅረማርያም አስማማው በበኩሉ ‹‹ችሎቱ ለአቃቤ ህግ ወገንተኝነት ያሳያል ብለን ስለምናምን ችሎቱ እንዲቀየርልን የጠየቅነው አቤቱታ ላይ ብይን ሳይሰጥ ጉዳያችንን ችሎቱ እንዳያይ ይደረግልን›› ሲል ተናግሯል፡፡ ችሎቱ አቤቱታው ለምን ለፕሬዝዳንቱ እንደቀረበ ግልጽ እንዳልሆነለት በመግለጽ አቤቱታው ለራሱ ለችሎቱም እንዲደርሰው ጠይቆ ከተከሳሾች እንዲደርሰው አድርጓል፡፡
በሌላ በኩል 4ኛ ተከሳሽ አቶ ደሴ ካህሳይ የትግርኛ ቋንቋ ተናጋሪ መሆናቸው ታውቆ አስተርጓሚ እንዲመደብላቸው ጠይቀው እንደነበር በመግለጽ እስካሁን አስተርጓሚ እንዳልተመደበላቸው ገልጸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች ባቀረቡት አቤቱታ ላይ ብይን ለመስጠት በሚል ለየካቲት 4/2008 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ በተወካዮች ምክር ቤት በአሸባሪነት የተፈረጀውን ግንቦት ሰባት የተባለ የፖለቲካ ድርጅት ለመቀላቀል ወደ ኤርትራ ሲያመሩ ማይካድራ የተባለ የድንበር ከተማ ላይ መያዛቸውን አቃቤ ህግ በክሱ ላይ አስፍሯል፡፡

ሰውየው ---ብርሃኑ ነጋ ( ሄኖክ የሺጥላ )

#‎በሄኖክ_የሺጥላ‬
ሰውየው ---ብርሃኑ ነጋ ( ሄኖክ የሺጥላ )
አጭር ፍቅር
ሰውየው ሕልም አለው ። የአንደበቱ ርትዖነት ካለው የቃላት አጠቃቀም እና ልቀት ሳይሆን የሚመነጨው ከሃሳቡ ጠጣርነት እና ከቆመለት ትልቅ እውነት እንጂ !
ሰውየው ሕልም አለው ፣ ለዚያውም በሞቀ ቤት እና በቀዘቀዘ ቢራ ውስጥ በሚደረግ የሳይበር ጦርነት የሚጸና ሳይሆን ፣ የማሽላ እንጀራ እየበላ አፈር ላይ እየተኛ ፣ ከእባብ እና ገጊንጥ ጋ እየተታገለ ፣ በሞርታር እና በፈንጂ ወረዳ ውስጥ ውድ ነብሱን አቁሞ የሚሞትለት እጹብ ሕልም ።...
ሰወየው ትሁት ነው ፣ የትልቅነት ሚስጥሩ ምን እንደሆነ የገባው ትሁት ። ሕልሙ ባለ ወፍራም ቆዳ ያደረገው እንደራሴ ፣ አላማው ለትንንሽ ነገሮች እና በትንንሽ ነገሮች ከማኩረፍ እና ከመኮፈስ ነጻ ያወጣው የኔ ዘመን በትረ አሮን ። በግልምጫ እና በእርግጫ ፖለቲካ ውስጥ ሊባክን የሚችል ታል-ኢት ( የሰኮንድ ግማሽ ) የሌለው ሰው ። ሰውየው አፋር ነው ሃገሩ ፣ ጎጃሜም ነው ፣ በኦሮሞነቱ አይታማም ፣ ጥርት ያለ ጉራጌ ነው ፣ ዘሩን የቆጠሩ ሱማሌ ስለመሆኑ ይናገራሉ ፣ አብረውት ያደጉት እና በቅርብ የሚያውቁት ስለመንዜነቱ የሚያውቁትን ሁሉ ሳይደብቁ ያወራሉ ፣ እርግጥ ሰውየው ኢትዮጵያዊ ነው ። ማነስ አይችልም ፣ በጎጥ እና በጎሳ ፣ በአውራጃ እና ወረዳ ፣ ተቆርሶ እና ተሰባብሮ የሚነገር ማንነትም ሆነ ፣ የሚቆጠር ደም የለውም ። ሕሉሙ ከደሙ ጋ አንድ አይነት ነው ፣ ትውልደ ኢትዮጵያዊ እና ዘረ ኢትዮጵያዊ ፣ ሰወየው !
ስለ ሰውየው ሳስብ ኩራት ይሰማኛል ፣ ምክንያቱም ኢትዮጵያዊነት እንደማይሞት ምሳሌ ሆኗልና ፣ ቃሉን አላጠፈምና ፣ የሚኖርለት ሰው ባይኖር እንኳ የሚሞትለት ክብር እና ነጻነት ያለው ስለሆነ ። በቅርቡ ዋሽንግተን ዲስ ባደረገው ንግግር " እዚህ ውስጥ ብዙ የማውቃችሁ ጓደኞቼን ወዳጆቼን አይቻለሁ ፣ ሁሌ አስባችሗለሁ ፣ ላናንተ ብዬ ግን ከምሄድበት አልቀርም " የምትለዋን ሐረግ ድግሜ ደጋግሜ አደመጥኩ ፣ በእድሜ የሱ እኩዮች የሆኑ ፣ እንደሱ ወይም ከሱ በላይ የተማሩ ፣ ሀገር ሀገር የሚሉ ግን አንዳች ቁም ነገር ያለው ሥራ መስራት ያልቻሉት ወዳጆቹ ምን ይሰማቸው ይሆን ? እነዚህ በጥላቻ እና በማጥላላት የፖለቲካ ቁማር የሰከሩ << የፖለቲካ ቁሞ ቀሮች >> ወይም ዊዶዎች ይህንን ሲሰሙ ምን ይሉ ይሆን ?
እርግጥ ይህንን ጽሑፍ የምታነቡ ሰዎች ማሽቃበጥ ሊመስላችሁ ይችላል ። እርግጥ አልተሳሳታቹም እያሽቃበጥኩ ነው!! ሰው እንኳን ለብርሃኑ ነጋ ለወያኔ ያሽቃብጥ የለ ። ታዲያ ምን ሽግር ኣለው ?
ሺዎች ከጎንህ ነን ። ከጎንህ ያቆመን ደሞ የቆምክለት አላማ ነው !

Wednesday, 3 February 2016

መለስ ሳይጠየቁ ሾለኩ

መለስ ሳይጠየቁ ሾለኩ
* በጋምቤላ የለኮሱት እሳት አሁንም እየነደደ ነው
* “የሟቾች ቁጥር እስከ መቶ ሊደርስ ይችላል” ነዋሪዎች
* “የሞቱት 14 ሰዎች ናቸው” ኢህአዴግ
ሰሞኑን በጋምቤላ በደረሰው የእርስበርስ ፍልሚያ እስከመቶ የሚጠጉ መሞታቸውን የክልሉ ነዋሪዎች ተናገሩ፡፡ ኢህአዴግ በበኩሉ የሞቱት 14 ብቻ ናቸው ይላል፡፡ ዘረኝነትንና ጠባብ ጎሰኝነትን ለኢትዮጵያ እንደ “ገጸ በረከት” ያመጡት መለስ በየቦታው የጫሩት እሣት ለፍርድ ሳያቀርባቸው ሾልከዋል፡፡ እሣቱ ግን አሁንም እየነደደ ነው፡፡
ጎልጉል ከአካባቢው ነዋሪዎችና ጉዳዩን በቅርብ ሲከታተሉ ባገኘው መረጃ መሠረት በግጭቱ የሞቱት እስከ መቶ እንደሚደርስ ይነገራል፡፡ ግጭቱ ከመነሻው በቀላሉ የተነሣ ቢሆንም ወዲያውኑ ወደከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ሥር የሰደደ ፖለቲካዊ ምክንያት እንዳለው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡ ይህንኑ ዜና ኢሳት ሲዘግብ የሟቾቹ ቁጥር ከመቶ እንደሚያልፍ ምንጮቹን ጥቅሶ አስታውቋል፡፡
ጸረ ቁጥር የሆነው ኢህአዴግ ወራትን ባስቆጠረው የተማሪዎች ዓመጽ ከሁለት መቶ በላይ ሞተው ሟቾች ከአስር ያልበለጡ ናቸው ከማለቱ በፊት መጀመሪያ ምንም የሞተ የለም፤ ቀጥሎም የሞቱት አምስት ናቸው ማለቱ ይታወሳል፡፡ አሁን ደግሞ የኢህአዴግ አፈቀላጤ ጌታቸው ረዳ በጋምቤላው ግጭት የሞቱት ቁጥሩን እርግጠኛ ለማስመሰል ይመስላል 14 ናቸው ብለዋል፡፡
አቶ መለስ በአዛዥነት ከሌሎች የህወሃት ሹማምንት ጋር በመሆን በሰጡት ቀጥተኛ ትዕዛዝ 424 የአኙዋክ ጎሣ አባላት በግፍ መጨፍጨፋቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱ የጭፍጨፋው አስፈጻሚ የነበሩት እና ኢህአዴግን ከድተው በውጪ አገር የሚገኙት የቀድሞው የክልሉ ኃላፊ ኦሞት ኦባንግ ኦሉም ከህወሃት ጋር ሆነው የተከሉት መርዝ ለሰሞኑ ግጭት መባባስ ምክንያት እንደሆነ ጉዳዩን የሚከታተሉ ወገኖች ይናገራሉ፡፡
በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) የዘር ጭፍጨፋ ከተካሄደባቸው በኋላ መሬታቸውን በግፍ ከተነጠቁት አኙዋክ ወገኖች መካከል ከዘር ማጥፋቱ ያመለጡት በበርካታ ሺዎች የሚቆጠሩት አገር ለቅቀው ተሰደዋል፡፡ በዓለምአቀፍ ድርጅቶች ዘንድ በቁጥር ደረጃ ለመጥፋት የተቃረቡ ከሚባሉት አኙዋኮች በህይወት የቀሩት ደግሞ አሁን ለዘር እንዳይቀሩ ሆነው እየተጨፈጨፉ ይገኛሉ፡፡ የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ግጭቱ እርስበርስ መሆኑ ነው፡፡
ከዚህ ሌላ ህወሃት ከደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ጋር ያለው “የጫጉላ ጊዜ” በማብቃቱ ለተቀናቃኛቸው ሬክ መቻር ግልጽ ድጋፍ እየሰጠ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ከዚህ አኳያ የኑዌር ተወላጅ የሆኑት ሬክ መቻር ወደ ጋምቤላ እንደፈለጉ ሲወጡና ሲገቡ መክረማቸውን ጎልጉል ከዚህ በፊት ዘግቦ ነበር፡፡ የመቻርን ኃይል ለመደገፍ ከጋምቤላ በርካታ ኑዌሮች ወደ ደቡብ ሱዳን ገብተው ከሳልቫ ኪር የዴንቃ አባላት ጋር ጦርነት መጋጠማቸውና ከሞቱት መካከልም “የመከላከያ ሠራዊት” አባላት ለመሆናቸው ማስረጃ ስለመገኘቱ ጉልጉል በተደጋጋሚ መረጃ ደርሶታል፡፡
አሁን በተከሰተው ግጭት ቀድሞውኑም የታጠቁት የኑዌር አባላት አሁን ደግሞ ከደቡብ ሱዳን ግጭት ጋር በተያያዘ የመቻር ኃይል ያስታጠቃቸው ድንበር እያለፉ በመዝለቅ በአኙዋኮች ላይ የሚያደርሱት ጥቃት አሁንም አልቆመም፡፡ የአኙዋክ ጎሣ አባላትም ራስን ከመከላከል ጀምሮ መልሶ እስከ ማጥቃት በሚያደርጉት ምት በገጠር ቀበሌዎች የሚገደሉት ንጹሃን ቁጥር እጅግ እየጨመረ መሄዱ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ለጎልጉል አስታውቀዋል፡፡
“ኢትዮጵያውያንን እንደ እህል በዘር ከረጢት እየሠፈረ ለዚህ ሁሉ ዓይነት ስቃይና መከራ እንዲሁም ለማያባራ የዘር ግጭት የዳረገው መለስ ነው፤ ወደ ህይወት ማምጣት ብችል አስመጥቼ ፍትህ እንዲበየን ማስደረግ እፈልግ ነበር፤ ሙት አይወቀስም ይባላል፤ ልክ ሊሆን ይችላል አባባሉ ግን ለመለስ አይሠራም፤ እኔ ፍትህ የጠማኝ ነኝ” በማለት የመረረ አስተያየቱን ለጎልጉል በውስጥ መስመር የሰጠው ወጣት ይናገራል፡፡
ህወሃትና መለስ በኢትዮጵያ የተከሉት የዘር ፖለቲካ በአገሪቱ በበርካታ ቦታዎች የማንነት ጥያቄ ከማስነሳት አልፎ የህይወት መስዋዕትነት እያስከፈለ ነው፡፡ እምቢባዮችን “ልክ እናስገባለን” በማለት እየፎከረ አገር በነጻ አውጪ ስም የሚገዛው ህወሃት፤ የህይወት ዑደቱን እስኪያጠናቅቅ “ባለ ራዕዩ መለስ” ያስቀመጡለትን “ራዕይ” በትጋት እያስፈጸመ ይገኛል፡፡
(http://www.goolgule.com/

Tuesday, 2 February 2016

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
ከአስመራ ወደ አሜሪካ ለአጭር ጊዜ ለሥራ ጉዳይ መጥተዋል የሚለውን ተከትሎ ካሁን በኋላ አይመለሱም ለሚለው አሉባልታ ምላሽ ሰጥተዋል:: ፕሮፌሰር ብርሃኑ እንዳሉት ከዚህ ‘ሲያምራችሁ ይቅር እኔ ከአሁን በኋላ ከዚህ ትግል አልርቅም” ብለዋል::“የብሔር ጥያቄን የመለሰች፤ ከራሷ ጋር የታረቀች ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን”– ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ ባደረጉት ሕዝባዊ ስብሰባ በኢትዮጵያ በተከሰተው ረሃብ; በኦሮሞ ተማሪዎች አመጽ እና ትግሉ ስላለበት ሁኔታ እንዲሁም ስለተቃዋሚዎች ተናግረዋል::
...
በኢትዮጵያ የተከሰተው ረሃብ የስርዓቱ ችግር ነው ካሉ በኋላ እርሳቸው የሚመሩት ተቋም ከዚህ ቀደም የገመተው የተራቢዎች ቁጥር አሁን ተግባራዊ እየሆነ እንደሆነ እንዲሁም ይህ አስተዳደር ከቀጠለ ከዚህ ቀደም እንደገመቱት በ2050 ዓ.ም 50 ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚራብ ገልጸዋል::
በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ዙሪያም እንዲሁ የተናገሩት ፕሮፌሰሩ በኦሮሚያ ክልል ህፃናት እና ነብሰጡርን ሳይቀር እየገደለ ያለውን ስርዓት ሕዝቡ እየሞተ ያለው ወገኔ ነው ብሎ ማውገዝ አለበት ብለዋል:: በተለይም በአሁኑ ወቅት ከኦሮሞ ድርጅቶች ጋር በህብረት ለመታገል ንግግሮች መጀመራቸውንም አስታውቀዋል::
ስለተቃዋሚዎችም የተናገሩት ፕሮፌሰሩ “የተቃዋሚዎች የምኞት ፖለቲካ ነው የሚከተሉት” ሲሉ ተችተው የምር መታገል እንዳለባቸው አስምረውበታል::
ወቅታዊውን የአርበኞች ግንቦት 7 ሁኔታ በተመለከተም “ወታደሮቻችን ያሉት ኢትዮጵያ ውስጥ ነው… ትግላችንን ለመቀላቀል ካሁን በኋላ ለምትፈልጉ ወደ ሰሜን ብቻ መሄድ የለባችሁም” ብለዋል::