ማር በሜንጫ ( ሄኖክ የሺጥላ )
እኛ ኢትዮጵያውያኖች ነን ፣ ስለዚህ እነ ሜንጫ ( <Ethiopia out of Oromoa> ) ሲሉን ፣ እንዴት ተደርጎ ? እንዴት ልጅ እናቷን ትወልዳለች ብለን ነበር ። እኛ የወያኔ በደልን የምንጠየፈው ወያኔ በዘር ተደራጅቶ አንድን ወይም ሁለትን ዘር ኢላማ አድርጎ የዘር ማጥፋት በየዕለቱ በመፈጸሙ ነው ፣ ይህንንም ስንል ወያኔን ( የኛን ቁስል የጠገበውን ዝንብ አራግፈን ሌላ ወያኔ መሳይ ፣ ቁስል የናፈቀው ዝምብ ይምጣ ማለታችን አይደልም ።) ይህንን ስንል በአሩሲ ፣ በባሌ ፣ በጉጂ ፣ በበደኖ ፣ በአርባባ ጉጉ እና ወዘተ የፈሰሰው የንጹሃን ኢትዮጵያውያን ደም ፍትሃዊ እና ሚዛናዊ የሕግ ፍርድ ስላገኘ አይደለም ዛሬ የኦሮሞ ልጆች ደም መፍሰስ የሚቆጨን ፣ ይህንን ስንል እስከሚገባኝ ያኛውም ይሁን ይሄኛው የዘር ማጥፋት ሴራ በበላይነት የተመራው በወያኔ መሆኑን ስለምንረዳ ፣ አትኩሮታችን ወያኔን ማስወገድ ላይ ይሁን ማለታችን ነው እንጂ ፣ የጠላታችን ጠላት ወዳጃችን ነው ማለታችን አይደለም ። የጠላታችን ጠላት ወድጃችን የሚሆነው የጋራ የሚያደርግ ነገር ሲኖረን ብቻ ነው ። የጋራ የሚያድረግ ስል ፣ የጠላታችን ጠላት ፣ አንቦ ላይ የተገደሉት የኦሮሞ ልጆች ጎንደር ላይ ከፈሰሰው የአማራ ልጆች ደም በምንም አይነት አይበልጥምም አያንስምም ብሎ ማመን ከቻለ ብቻ ፣ የሱ የእንተባበር ጥሪ ሰሚ ያገኛል ። ይህም ማለት አንቦ ላይ ለሚፈሰው ደም እሱ ሕጋዊ ወኪል ወይም ተጠሪ ነው ማለት አይደለም ፣ ወይም ደም ጎንደር ላይ ለፈሰሰው ደም አማራው ብቻ የሚባዝንበት እና በበላይነት የሚመራው የብቻ ኃላፊነት ነው ማለት አይደለም ። ግን ደሞ ፣ ያንተ ቁስል የነፍጠኛ ቁስል ነው ፣ የኔ ግን ዘላለም ሲብደል የኖረ ሕዝብ ቁስል ነው የሚለኝ ከሆነ < ብቻውን ቁስሉን ሲያክ ሊኖር ነው ማለት ነው !> ፣ < በዚህም ጎን እንደዚያው !>
ለዚህም ነው ሰሞኑን ጃዋር መሐመድ በ (ኦሮሞ ሚዲያ ኔትወርክ ( OMN )) ቀርቦ ያደረገውን የእንተባበር ጥሪ ፣ ከጉንጫ አልፋ ፖለቲካና ፣ የመለዜናው ቃናን ከያዘ ብልጣ-ብልጥ የአፍ ፖለቲካ ባሻገር ፣ < ወይም ማር የተለወሰ መርዝ > እንደሆነም አድርጌ ያየሁት ።
በመሰርቱ ውይይቱ ራሱ ብዙ ግድፈት የበዛበት ነው ። ለምሳሌ ጃዋር < ኢትዮጵያ ውስጥ የኢኮኖሚ እድገት እናዳለ ይናገራል ፣ በኦሮሚያ አካባቢ ያሉ ገበሬዎች የተራቡት መሬታቸው በመንግስት ስለተነጠቀ ነው ይላል ፣ በአማራ ክልል አንድ ሄክታር መሬት አልተወረሰም ፣ ወይም ለባለሃብት በኢንቨስትመን ስም/ምክንያት አልተሰጠም ይላል ? ይህንን ያለው ስለ ወልቃይት ጠገዴ ስለማያውቅ አይደለም ፣ ጎንደር ላይ ዛሬ ድንበር ተካሎ ለሱዳን ተቆርሶ ሊሰጥ እንደሆነ ስለማያውቅ አይደለም ፣ በሁመራ ሰሊጥ ፣ ጥጥ ፣ እጣን እና ኑግ እየዘራ የምያጭደው ወያኔ እንደሆነ ስለማይረዳ አይደለም ፣ ባጭሩ ለጃዋር አማራው ላይ የሚደርሰው በደል በደል ሆኖ ስለማይታየው ነው ፣ ስለዚህ
አባት ዓለም ባለቅኔው ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ያለውን ለጃዋር ላስታውሰው
የት ሊደረስ
ዛሬ ሀቅ ቢቀለበስ
በጀርባችን ይከተላል ነገ የዳኝነት ፈረስ
ዛሬ ሀቅ ቢቀለበስ
በጀርባችን ይከተላል ነገ የዳኝነት ፈረስ
መቻቻልን ማወቅ ነው እንጂ
ጠንቅቀን እንደ አባ መቻል
መሸቀል አይሰራም በቃል !
ጠንቅቀን እንደ አባ መቻል
መሸቀል አይሰራም በቃል !
ዛሬ ጮሌ ሆኗል ሁሉም
ብልህነት እንጂ ብልጠት
አክትሞለታል ዘመኑም !
ብልህነት እንጂ ብልጠት
አክትሞለታል ዘመኑም !
ስለዚህ ይገባናል ፣ ይህ የእንተባበር ጥር ከልብ የመነጨ እንዳልሆነ ። እንደ ጃዋር አባባል < እኛ በኦሮሞ ምድር ሌላ ሰው አይኑር አላልንም ! እንደውም ሰው እንፈልጋለን !> ይላል ። ይህ ልክ ከሆነ ( <Ethiopia out of Oromoa> ) ያለውን ጃዋር እንመን ወይስ ይሄ ሰው እንፈልጋለን ያለውን ። ወይስ ሰው የሚፈልገው ከደማስኮ ይሆን ? በመጀመሪያ ጃዋር የኢትዮጵያን ሕዝብ ለትብብር ለመጠየቅ የሚያስችል የሞራል ብቃት አለው ብዬ አላምንም።
እንድንተባበረው ከፈለገ ፣ እንደ ሕዝብ ይቅርታ ሊጠይቀን ይገባዋል ፣ ዝቶብናል ፣ ፈርጆናል ፣ እንደውም በሜንጫ ( እንደሱ አባባል መንጫ ማለት እንደ ቦክስ ነው ፣ በቦክስ ሊለን ዝቷል !) ። ያለበለዚያ ጃዋር ሆይ ያንተ ይቺ እንተባበር ጥሪ ማር በ -ሜንጫ ላሱ ነገር ትመስላለች ፣ ሙድ የላትም!!!
የግርጌ ማስታወሻ
ጃዋርን ያላማከረ እና ያላማከለ ለኢትዮጵያውያኖች ( ኦሮሞዎች ፣ አማራዎች ፣ ጉራጌዎች እና ወዘተ ) የሚደረግ የተቃውሞ ና የትግል ጥሪ ያስፈልጋል እያልኩ አይደለም ። እያልኩ ያለሁት የትግሉ ብሌን መሆን የሚፈልገው ጃዋር እና መሰሎቹ ከራሳቸው ባህሪ ስንነሳ ሕዝብ ሊከተላቸው ወይም ሊሰማቸው የሚችሉ ሰዎች አይደሉም ( ሕዝብ ስል የኢትዮጵያ ሕዝብ ማለቴ ነው )። ይልቁንም ሌላ ህውሃት ፣ ሌላ ገዳይ ቡድን ፣ የተፈጠረውን እሳት ተጠቅሞ ፣ ከቻለ ይህ " አማርኛ ሲሰማ የተወደደ የሚመስለው የዋህ አማራ ካለ ፣ እሱን አበድኖ ፣ ወንድምህ ነኝ ብሎ ፣ ትግል መንግሎ ለመቆም የሚያደርጉት ብልጣ ብልጥነት ነው !" የጃዋር የለበጣ አማርኛ ሆድ የሚያስብሰው ካለ የራሱ ጉዳይ ነው ፣ እኔ ግን ስለ ጃዋር ሳስብ ጭንቅላቴ ውስጥ የሚመጣው ሜንጫው ነው !
ጃዋርን ያላማከረ እና ያላማከለ ለኢትዮጵያውያኖች ( ኦሮሞዎች ፣ አማራዎች ፣ ጉራጌዎች እና ወዘተ ) የሚደረግ የተቃውሞ ና የትግል ጥሪ ያስፈልጋል እያልኩ አይደለም ። እያልኩ ያለሁት የትግሉ ብሌን መሆን የሚፈልገው ጃዋር እና መሰሎቹ ከራሳቸው ባህሪ ስንነሳ ሕዝብ ሊከተላቸው ወይም ሊሰማቸው የሚችሉ ሰዎች አይደሉም ( ሕዝብ ስል የኢትዮጵያ ሕዝብ ማለቴ ነው )። ይልቁንም ሌላ ህውሃት ፣ ሌላ ገዳይ ቡድን ፣ የተፈጠረውን እሳት ተጠቅሞ ፣ ከቻለ ይህ " አማርኛ ሲሰማ የተወደደ የሚመስለው የዋህ አማራ ካለ ፣ እሱን አበድኖ ፣ ወንድምህ ነኝ ብሎ ፣ ትግል መንግሎ ለመቆም የሚያደርጉት ብልጣ ብልጥነት ነው !" የጃዋር የለበጣ አማርኛ ሆድ የሚያስብሰው ካለ የራሱ ጉዳይ ነው ፣ እኔ ግን ስለ ጃዋር ሳስብ ጭንቅላቴ ውስጥ የሚመጣው ሜንጫው ነው !
No comments:
Post a Comment