ግርማ ሰይፉ ማሩ
"ኦሮሞ ያልሆነ የኦሮሞ ችግር አይገባውም፣ ድሮም ከአበሻ ምን ይጠበቃል፣ የእኔ እና የሌሎች ሃሳብ የሚል ፖለቲከኛ፣ አንተን ብሎ ፖለቲከኛ የሚሉና የሚመሳስሉ ብዙ ምላሾች አንብቢያለሁ፡፡ ለማነኛውም ልዮነታችን ከፍልሰፍናችን እንደሚመነጭ ተረድቻለሁ፡፡ እኔ በቡድን አስተሳሰብ ውስጥ የለሁበትም፡፡ ብዙ ሰው /ህዝብ የሚባልም ቢሆን/ ስለደገፍ ያለመደገፍ መብት አለኝ፡፡ ማስረጃ ላቅርብ በምክር ቤት 546 ሰው ሲደግፍ ብቻዬን ተቃውሚያለሁ፡፡ ብዙ በደገፈ መደገፍ ከሆነ ይህንንም መደገፍ ሊኖርብኝ ነው፡፡ ይህ ግን አይሰራም፡፡ ለማነኛውም ጉዳዮን ከረር ለማረግ እኔ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ይህ የእኔ ብሔር መሬት፣ ሀብት፣ ወዘተ የምለው የለኝም፡፡ ለእኔ የሌለኝ ሌሎች መብት ሌሎች ያላቸው አይመስለኝም፡፡ ነገር ግን ሌሎች እንዲኖራቸው መፈለግ መብታቸው... ቢሆንም ህጋዊ ግን አይደለም፡፡ ለምሳሌ መሬት በግለሰብ ደረጃ በሚሰጥ ካርታ እንጂ በዘር በጎሳ በሐይማኖት የሚያዝ አይደለም፡፡ ህገ መንግሰቱ ካሉበት ሸፋፋ ነገሮች አንዱ መሬት የህዝብና የመንግሰት ነው የሚለው ክፍል ነው፡፡ እንበል “የኦሮሞ መሬት” የሚባል አለ ከተባለ፣ ይህ መሬት ለወላይታ እንዴት ሊሰጥ ይችላል? በአዋሳ ከተማ ያለ መሬት የሲዳማ ከሆነ ካርታ የያዙ ሌሎች ሰዎች ባለመብት አይደሉም ማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ “ብሔር፣ ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች” በሰማቸው ካርታ ያላቸው አይመሰለኝም፡፡ ካላቸው እንደመረጃ ፖሰት አድርጉልኝ፡፡ ማንም ደስ ቢለው ቢከፋው እኔ የተመቸኝ ሃሳብ “ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ አማርኛ፣ ወዘተ የሚባሉ ቋንቋ እንጂ የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የትግሬ፣ ወዘተ የሚባል መሬት የለም” የሚለው ነው፡፡ በህገ መንግሰት ማንም ሰው በፈለገበት የመኖርና የመስራት፣ ንብረት የማፍራት መብት እንዳለው ሲገልፅ በዘር የሚገኝ ንብረት፣ ሀብት የሌለ መሆኑን ለማስቀመጥ ይመስለኛል፡፡ ለማነኛውም አንተ ብሎ ፖለቲከኛ ላላችሁኝ መቼ አልኩ እኔ እናንተ አላችሁኝ እንጂ ማለት ነው፡፡ የአኔን ፖለቲካም ሆነ ማህብራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ አስተያየት መውደድም ሆነ መጥላት መብት ነው፡፡ ለማንኛው እወዳችኋለሁ … ገለቶማ!"
"ኦሮሞ ያልሆነ የኦሮሞ ችግር አይገባውም፣ ድሮም ከአበሻ ምን ይጠበቃል፣ የእኔ እና የሌሎች ሃሳብ የሚል ፖለቲከኛ፣ አንተን ብሎ ፖለቲከኛ የሚሉና የሚመሳስሉ ብዙ ምላሾች አንብቢያለሁ፡፡ ለማነኛውም ልዮነታችን ከፍልሰፍናችን እንደሚመነጭ ተረድቻለሁ፡፡ እኔ በቡድን አስተሳሰብ ውስጥ የለሁበትም፡፡ ብዙ ሰው /ህዝብ የሚባልም ቢሆን/ ስለደገፍ ያለመደገፍ መብት አለኝ፡፡ ማስረጃ ላቅርብ በምክር ቤት 546 ሰው ሲደግፍ ብቻዬን ተቃውሚያለሁ፡፡ ብዙ በደገፈ መደገፍ ከሆነ ይህንንም መደገፍ ሊኖርብኝ ነው፡፡ ይህ ግን አይሰራም፡፡ ለማነኛውም ጉዳዮን ከረር ለማረግ እኔ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ይህ የእኔ ብሔር መሬት፣ ሀብት፣ ወዘተ የምለው የለኝም፡፡ ለእኔ የሌለኝ ሌሎች መብት ሌሎች ያላቸው አይመስለኝም፡፡ ነገር ግን ሌሎች እንዲኖራቸው መፈለግ መብታቸው... ቢሆንም ህጋዊ ግን አይደለም፡፡ ለምሳሌ መሬት በግለሰብ ደረጃ በሚሰጥ ካርታ እንጂ በዘር በጎሳ በሐይማኖት የሚያዝ አይደለም፡፡ ህገ መንግሰቱ ካሉበት ሸፋፋ ነገሮች አንዱ መሬት የህዝብና የመንግሰት ነው የሚለው ክፍል ነው፡፡ እንበል “የኦሮሞ መሬት” የሚባል አለ ከተባለ፣ ይህ መሬት ለወላይታ እንዴት ሊሰጥ ይችላል? በአዋሳ ከተማ ያለ መሬት የሲዳማ ከሆነ ካርታ የያዙ ሌሎች ሰዎች ባለመብት አይደሉም ማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ “ብሔር፣ ብሔረሰቦች፣ ሕዝቦች” በሰማቸው ካርታ ያላቸው አይመሰለኝም፡፡ ካላቸው እንደመረጃ ፖሰት አድርጉልኝ፡፡ ማንም ደስ ቢለው ቢከፋው እኔ የተመቸኝ ሃሳብ “ኦሮምኛ፣ ትግርኛ፣ አማርኛ፣ ወዘተ የሚባሉ ቋንቋ እንጂ የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የትግሬ፣ ወዘተ የሚባል መሬት የለም” የሚለው ነው፡፡ በህገ መንግሰት ማንም ሰው በፈለገበት የመኖርና የመስራት፣ ንብረት የማፍራት መብት እንዳለው ሲገልፅ በዘር የሚገኝ ንብረት፣ ሀብት የሌለ መሆኑን ለማስቀመጥ ይመስለኛል፡፡ ለማነኛውም አንተ ብሎ ፖለቲከኛ ላላችሁኝ መቼ አልኩ እኔ እናንተ አላችሁኝ እንጂ ማለት ነው፡፡ የአኔን ፖለቲካም ሆነ ማህብራዊ እንዲሁም ኢኮኖሚያዊ አስተያየት መውደድም ሆነ መጥላት መብት ነው፡፡ ለማንኛው እወዳችኋለሁ … ገለቶማ!"
No comments:
Post a Comment