መሳይ መኮንን
ህወሀት ''ቅማንት'' የሚል አደገኛ ካርድ ስቧል። በኢትዮጵያ ምድር ላይ ተፈጽሟል ለማለት የሚከብድ እጅግ ዘግናኝ ድርጊት ተፈጽሟል። የማንነት ጥያቄ ተገቢ ቢሆንም በህወሀቷ ኢትዮጵያ ግን ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ የሚያመዝን ነው። የዲሞክራሲ ጥያቄ ባልተመለሰበት ሁኔታ፡ የማንነት ጥያቄ የጨቋኞችን ዕድሜ የሚያራዝም መድሃኒት ነው። ህወሀት ዲሞክራሲን ሊያመጣ ፈጽሞ የሚችል ድርጅት አይደለም። አፈጣጠሩና እወክለዋለሁ የሚለው ህዝብ የአናሳ ቁጥር ያለው በመሆኑ ከዲሞክራሲ መርህ(Majority rule-Minority right) ጋር የሚጻረር ነው።ቢፈለግ እንኳን አይቻለውም።
ለዚህም ነው የማንነት ጥያቄን በየቦታው እየቀሰቀሰ ህዝብን ከህዝብ እያናከሰ በስልጣን ላይ መቆየትን የመረጠው። እንዲህ አድርገን ካልገዛን በቀር ስልጣን ላይ መቆየት አንችልም ብለው ሟ...ቹ ጠቅላይ ሚኒስትር በድብቅ የተናገሩት እንዳለ ነገ ከነገ ወዲያ ይጋለጣል።
እናም ህወሀት ዘንድሮ የሳባት የቅማንት ካርድ መጥፎ አየር ይዛ መጥታለች። በጣም አሰቃቂ በሆነ መልኩ የተገደሉ ኢትዮጵያውያን ቪዲዮ በማህበራዊ መድረኮች ተለቋል። ተመልክቼው ራሴን መቆጣጠር እስኪያቅተኝ ደንግጬአለሁ። ከመነሻው ሂደቱን ስንከታተል ስለነበረ ማን ከዚህ አሰቃቂ ድርጊት ጀርባ እንዳለ በሚገባ ተረድተነዋል። ኢትዮጵያውያን ከምንጊዜውም በላይ ጥንቃቄ ልናደርግ የሚገባን ግዜ ላይ ደርሰናል። ድንበሩን ለማስረከብ በመጪው ወር ቀጥሮ ተይዟል። በጎንደር ዘግናኝ ድርጊት እየተፈጸመ ነው።
እነዚህ ሁለት ክስተቶች በአንድ ወቅት ላይ እንዲሆኑ የተደረገው ያለምክንያት አይደለም። ስለድንበሩ ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ድምጹን እንዳያሰማ በመንደርና ጎጥ ተከፋፍሎ ሁሉም በየሰፈሩ እርስ በእርሱ እየተጠባበቀ፡ አጥር ሰርቶ፡ እየተደገዳደለ እንዲኖር አድርገውታል። በድንበሩ ጉዳይ ከሱዳንና ከህወሀት ወታደሮች ጋር እየተዋጋ የከረመው ይኧው የጎንደሩ ኢትዮጵያዊ ነው። ይህ ህዝብ ለድንበር ማካለሉ እንቅፋት እንዳይሆን ደግሞ ህወሀት ሌላ ካርድ ስቧል። የቅማንት የማንነት ጥያቄ። ጥያቄው ተገቢ አይደለም እያልኩኝ አይደለም። በህወሀት ተቀናብሮ ይህን ጊዜ ጠብቆ መነሳቱ እንጂ።
ጎንደር ሰሞኑን በተከሰተው ዘግናኝ ድርጊት ተወጥራለች። ለመጪው ሌላ የዕልቂት ዳመና አርግዟል። በመሃል የድንበሩ ማካለል ተፈጻሚ ይሆናል። ምን ይበጃል?
ድንበሩ የጎንደር ብቻ አይደለም። በስለት ተከታትፎ እየተገደለ ያለው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ነው። እኔ እዚህ ቪዲዮውን መለጠፍ አልፈለኩትም። በየቦታ ስላለ ማየት የሚቻል ይመስለኛል።
ኢሳት ይህን የህወሀት የዕልቂት ድግስ ለማክሸፍ የሚቻለውን ያደርጋል። እንደ ዜጋ፡ እንደ ኢትዮጵያዊ፡ ከምንም በላይ እንደ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር፡ እኔም አቅሜና ሙያዬ በሚሰጠኝ ጉልበትና ዕድል ተጠቅሜ ይህን ኢትዮጵያውያን ላይ የተወረወረውን የጥፋት ሰይፍ ለመመከት ቃል እገባለሁ። ጎበዝ እንደ ትውልድ የምንፈተንበት ዘመን ላይ ነን። መሃሉ ላይ ነን። ወጀብ ከግራና ቀኝ ይዞናል። ተያይዘን ካልወጣን መሃሉ ላይ እንቀራለን። .....ፈጣሪ ኢትዮጵያችንን ይታደጋት!!!!
Sunday, 29 November 2015
Saturday, 28 November 2015
አርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም ከሳሽም ምስክርም ሆኖ ፍ/ቤት ቀረበ
አንጋፋው ተዋናይ አርቲስት ፍቃዱ ተ/ማርያም በሽርክና የሚያሳትመውን የመረጃና የስልክ አድራሻ ማውጫ ዳይሬክተሪ፤ አመሳስለው በማዘጋጀት ለገበያ አቅርበውብኛል ባላቸው አካላት ክስ መስርቷል “እንደ ልጄ የማየውን ሥራዬን ነው የወሰዱብኝ” ብሏል – አርቲስቱ፡፡

ተከሳሹ የንግድ ፍቃድ ሳይኖራቸው ዳይሬክተሪውን አሳትመው ማሰራጨታቸውም በክሱ ተጠቅሷል፡፡ አቃቤ ህግ 7 የሰው ምስክሮችና የሰነድ ማስረጃዎችን ያቀረበ ሲሆን ባለፈው ማክሰኞ ሰባቱም ምስክሮች ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡
ከአቃቤ ህግ ምስክሮች አንዱ ሆነው የቀረቡትና በአርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም የኪነ ጥበብና ማስታወቂያ ድርጅት ውስጥ የ50 በመቶ ድርሻ ያላቸው ኢ/ር ብስራት ዳንኤል በሰጠው ቃል የዳይሬክተሪውን ሙሉ የመረጃ ቅንብር (ዳታ ቤዝ) እሳቸው እንዳዘጋጁት ጠቁመው፣ ተከሳሽ የመረጃ ቅንብራቸውን ሙሉ ለሙሉ በመገልበጥ ማሳተማቸውን ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ ከተመሰረተ ጀምሮ 4 ተከታታይ ህትመቶችን ማውጣቱን የገለፁት ምስክሩ፤ የተወሰደባቸው የመረጃ ቅንብር ለ2012/13 እ.ኤ.አ ያዘጋጁት ሲሆን ተከሳሹ ለ2014/15 በሚል ወቅታዊ አድርገው ማሳተማቸውን አስረድተዋል፡፡
ሐምሌ 20 ቀን 2006 ዓ.ም ህትመቱን ከቻይና ወደ ሀገር ውስጥ ያስገቡት ተከሳሹ፤ ነሐሴ 14 ቀን 2006 ዓ.ም ከጉምሩክ በማስወጣት፣ ማሰራጨት መጀመራቸውን ምስክሩ ጠቅሰው ለተለያዩ ድርጅቶች በአጠቃላይ በ117ሺ ብር አሰራጭተዋል ብለዋል፡፡ የተከሳሹ ዳይሬክተሪ በድርጅታቸው ከሚታተመው ዳይሬክተሪ ጋርም በስያሜ፣ ውስጥ ባሉ መረጃዎችና አቀማመጣቸው፣ በወረቀትና ቀለም አጠቃቀምና በማስታወቂያ አቀማመጥ እንደሚመሳሰሉ ተናግረዋል፡፡
ተከሳሹ፤ በአርቲስት ፍቃዱ ድርጅት ውስጥ የሽያጭ ሰራተኛ አስተባባሪ ሆነው ይሰሩ እንደነበር ያስታወሱት ምስክሩ፤ በ2002 ከድርጅቱ ከወጡ በኋላ ወረቀትና የወረቀት ውጤቶችን የማስገባት ፍቃድ እንጂ የማስታወቂያ ስራ ፍቃድ ሳይኖራቸው ነው ዳይሬክተሪውን ያሳተሙት ሲሉ ለፍ/ቤቱ አብራርተዋል፡፡ ተከሳሹ ጉዳዩ በፍ/ቤት ተይዞ ሳለም ሁለተኛ ህትመት ማሳተማቸውንም ምስክሩ ተናግረዋል፡፡
ሁለተኛ የአቃቤ ህግ ምስክር ሆኖ የቀረበው ራሱ አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ሲሆን፤ “ከቲያትር ስራ ጡረታ ከወጣሁ በኋላ መጦሪያዬ ይሆነኛል ያልኩትንና እንደ ልጄ የማየውን ስራዬን ነው ተከሳሽ የወሰዱብኝ” ብሏል፡፡ “ስምንት ዓመት የለፋንበትን ነው ገልብጠው ያሳተሙብን” ያለው ምስክሩ፤ ስራችን የመንግስት አካላት ተገቢ እውቅና የሰጡበት ነው ብሏል፡፡
ፍ/ቤቱ የአቃቤ ህግ ምስክሮችን በሙሉ ካደመጠ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከሉ በማለት ምስክሮችን ለመስማት ለጥር 3 ቀን 2008 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡
ከአቃቤ ህግ ምስክሮች አንዱ ሆነው የቀረቡትና በአርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም የኪነ ጥበብና ማስታወቂያ ድርጅት ውስጥ የ50 በመቶ ድርሻ ያላቸው ኢ/ር ብስራት ዳንኤል በሰጠው ቃል የዳይሬክተሪውን ሙሉ የመረጃ ቅንብር (ዳታ ቤዝ) እሳቸው እንዳዘጋጁት ጠቁመው፣ ተከሳሽ የመረጃ ቅንብራቸውን ሙሉ ለሙሉ በመገልበጥ ማሳተማቸውን ተናግረዋል፡፡ ድርጅቱ ከተመሰረተ ጀምሮ 4 ተከታታይ ህትመቶችን ማውጣቱን የገለፁት ምስክሩ፤ የተወሰደባቸው የመረጃ ቅንብር ለ2012/13 እ.ኤ.አ ያዘጋጁት ሲሆን ተከሳሹ ለ2014/15 በሚል ወቅታዊ አድርገው ማሳተማቸውን አስረድተዋል፡፡
ሐምሌ 20 ቀን 2006 ዓ.ም ህትመቱን ከቻይና ወደ ሀገር ውስጥ ያስገቡት ተከሳሹ፤ ነሐሴ 14 ቀን 2006 ዓ.ም ከጉምሩክ በማስወጣት፣ ማሰራጨት መጀመራቸውን ምስክሩ ጠቅሰው ለተለያዩ ድርጅቶች በአጠቃላይ በ117ሺ ብር አሰራጭተዋል ብለዋል፡፡ የተከሳሹ ዳይሬክተሪ በድርጅታቸው ከሚታተመው ዳይሬክተሪ ጋርም በስያሜ፣ ውስጥ ባሉ መረጃዎችና አቀማመጣቸው፣ በወረቀትና ቀለም አጠቃቀምና በማስታወቂያ አቀማመጥ እንደሚመሳሰሉ ተናግረዋል፡፡
ተከሳሹ፤ በአርቲስት ፍቃዱ ድርጅት ውስጥ የሽያጭ ሰራተኛ አስተባባሪ ሆነው ይሰሩ እንደነበር ያስታወሱት ምስክሩ፤ በ2002 ከድርጅቱ ከወጡ በኋላ ወረቀትና የወረቀት ውጤቶችን የማስገባት ፍቃድ እንጂ የማስታወቂያ ስራ ፍቃድ ሳይኖራቸው ነው ዳይሬክተሪውን ያሳተሙት ሲሉ ለፍ/ቤቱ አብራርተዋል፡፡ ተከሳሹ ጉዳዩ በፍ/ቤት ተይዞ ሳለም ሁለተኛ ህትመት ማሳተማቸውንም ምስክሩ ተናግረዋል፡፡
ሁለተኛ የአቃቤ ህግ ምስክር ሆኖ የቀረበው ራሱ አርቲስት ፍቃዱ ተክለማርያም ሲሆን፤ “ከቲያትር ስራ ጡረታ ከወጣሁ በኋላ መጦሪያዬ ይሆነኛል ያልኩትንና እንደ ልጄ የማየውን ስራዬን ነው ተከሳሽ የወሰዱብኝ” ብሏል፡፡ “ስምንት ዓመት የለፋንበትን ነው ገልብጠው ያሳተሙብን” ያለው ምስክሩ፤ ስራችን የመንግስት አካላት ተገቢ እውቅና የሰጡበት ነው ብሏል፡፡
ፍ/ቤቱ የአቃቤ ህግ ምስክሮችን በሙሉ ካደመጠ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከሉ በማለት ምስክሮችን ለመስማት ለጥር 3 ቀን 2008 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡
Addis Admass
Friday, 27 November 2015
የሴም ዘር ማን ነው? የኩሽ ዘርስ የቱ ነው? ሐበሻ የሚባሉትስ እነማን ናቸው?
በከተማ ዋቅጅራ
ኢትዮጵያ ውስጥ አንዱ ከአንዱ የተለያየን አድርጎ ማቅረብ አሁን አሁን በሰፊው እየተሰማ ነው። ኢትዮጵያ ብዙ የሚባሉ የታሪክ ሙሁራን ቢኖራትም ሙህራኑ በአገር ጉዳይ በያገባኛል መንፈስ በአንድነት ተሰባስበው ከመመካከር እና ከማስተማር ይልቅ ዝምታን መርጠዋል። የኢትዮጵያን እውነተኛውን ታሪክ ለህዝባቸው ከማሳወቅ ችልተኝነት ማሳየታቸው ኢትዮጵያ እንድትፈራርስ እየሰራ ያለው ወያኔ ያስደስት ይሆናል። ወያኔ አሁን አሁን እየተከተለ ያለው የአረብ አብዮትን ነው። አረቦች ጥያቄአቸው እንዲመለስላቸው የሚፈልጉት በሁከት ነው። ግዛታቸውንም ማስከበር የሚፈልጉት በሁከት ነው። ሃሳባቸውን ሌላው እንዲቀበላቸው የሚፈልጉት በማስፈራራት እና በሁከት ነው። እየገደሉ ሞተብን ብለው ይጮሃሉ እያፈነዱ አፈነዱብን ብለው ይናገራሉ በሁሉ ነገር በደል ፈጻሚ ቀዳሚዎቹ እነሱ ሆነው ሳለ ምላሽ የሚሰጣቸውን አገር አረብን ሊያጠፋ ነው ብለው ሁሉም እንዲነሱላቸው ማሳደም መቀስቀስ ይጀምራሉ አንድ ችግር ሲያጋጥማቸው ይሄንን ያደረሱብን እንደዚህ የምትባል አገር እና እንደዚህ የተባሉ አገር ናቸው ብለው በራሳቸው የተፈጠረውን ጥፋት ከማመን ይልቅ ወደሌላ አገር ላይ በመለጠፍ አረብ አገር በሙሉ እና ወዳጅ አገሮታቸውን ጥላቻ እንዲቀረጽባቸው አድርጎ መመረዝ ነው። ወያኔም እየሄደበት ያለው አካሄድ ይሄንኑ ነው።
ኢትዮጵያ መሽቶ በነጋ ቁጥር አዳዲስ ነገሮችን የሚሰማባት አገር ሆናለች። እድሜ ለወያኔ በዘር ፐውዞ ፐውዞ አንተ አበሻ ነው እኔ አበሻ አይደለሁም። አንተ ሴም ነህ እኔ ኩሽ ነኝ። አንተ እንደዚህ ነህ እኔ እንደዚ አይደለሁም። አንተ ከገሌ ወገን ነህ እኔ ከእገሌ ወገን አይደለሁም የሚል ጫጫታ በስፋት እየተሰማ ይገኛል። ይህም የሆነበት ዋናው ምክንያት የተማረው እና ታሪክ ጠንቅቀው የሚያውቁት ሙህራኖች በአንድላይ ተሰባስበው ስለ አገር በማሰብ የተለያዩ መድረኮችን በመፍጠር እውነተኛውን ታሪካችንን ከማስተማር እና ከማሳወቅ ይልቅ ዝምታን በመምረጣቸው የተነሳ ወያኔ እና መድረኩን የፈቀደላቸው የማያውቁትን ታሪክ የየራሳቸውን ሃሳብ በማንጸባረቅ በተደጋጋሚ እየተነገረ እና በመጽሃፍም ጭምር እውነትነት የሌለው ታሪክ አስመስለው እየተጻፉ በመሆኑ እንደዚህ የተዛቡ ታሪኮች ሲነገር በአጉል ተስፋ ሰዎችን ስለሚሞላቸው የኢትዮጵያን ታርክ የኛ ታሪክ አይደለም ብለው እስከማመን እያደረሳቸው ነው። በዚህ የተነሳ የኛ ታሪክ ወድቋል፣ ጠፍቷል፣ ተሰርዟል፣ ተረግጧል…… ሌላም ሌላም እየተባለ ስለሆነ እውነተኛ ታሪክን እያፋለሱ ያሉትን ሰዎች ወደ ሚዲያው በማውጣት ከታሪክ ሙሁራኑ ጋር ፊት ለፊት በማገናኘትና በማነጋገር ኢትዮጵያን የማዳኑን ስራ ትሰሩ ዘንድ ጋዜጠኞች ትልቅ ድርሻም አደራም አለባችሁ።
ሴም ወይንም ሴሜቲክ ማን ነው? ኩሽ ወይንም ኩሸቲክ ማን ነው? ሐበሻ የሚባሉትስ እነማን ናቸው? የሚለውን እንመልከት
ኖህ፡- ሴም፣ ካም፣ እና ያፌትን ወለደ ዘፍጥረት ፲+ ፩-፴፪ (10+1-32)
ሴም፡- ኤላም፣ አሦር፣ አርፋክስድ፣ ሎድ፣ አራም፣ ቃይናን ወለደ።
ካም፡- ኩሽ፣ ምስራይም፣ ፍጥ፣ ከነዓን ወለደ።
ያፌት፡- ጋሜል፣ ማጎግ፣ ማዴ፣ ያህያን፣ ያልሳ፣ ቶቤል፣ ሞሳሕ፣ ቴራስን ወለደ።
ከላይ የዘረዝርኳቸው የኖህ ልጆች እና የኖህ የልጅ ልጆች የሆኑ ናቸው።
ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ በሆነ የዘር መጠላለፍ የሚታየው ይሄንን እውነት ካለመረዳት ነው። ሴም በሉት ሴመቲክ ኩሽ በሉት ኩሸቲክ ለሴም አባቱ ለኩሽ አያቱ የሆነው ኖህ ነው። ታዲያ የአንድ ዘር ግንድ የሆንን ወንድማማቾች ይሄንን ያህል መጠላላት እና መለያየት ለምን አስፈለገ? ዛሬ ሴሜቲክ ነን እያልን የምንፎክር ዛሬ ኩሸቲክ ነን ብለን የምንፎክር አባታችን አንድ እንደሆነ ሲነገረን መደምደሚያችን ኖህ እንደሆነ ስናውቅ ምን ይሆን መልሳችን። ከየት ተነስተን ወደ የት ነው የምንሄደው? ወዴየትስ ነው መሄድ የምንፈልገው? ከማንስ ተፈጥረን ነው የሌላ ነን የምንለው ዛሬ እኛ ሴም ነን እኛ ኩሽ ነን ብለን የምንናገረው የተፈጥሮ ዑደታችን እውነቱ ይሄ ነው። ለዚህ ነው ብንጣላ የማንኮራረፈው ብንሰዳደብ የማንራራቀው የአንድ ቤተሰብ ልጆች ስለሆንን ነው። ነገሮችን ጠለቅ ብለን ስናውቅ ማንነታችንን እናውቀዋለን ማንነታችንን ስናውቅ ታሪካችንን እንወዳለን ታሪካችንን ስንወድ አገራችንን እንገነባለን አገራችንን ስንገነባ ለአለም ሁሉ የፍቅር፣ የሰላም የአንድነት የስልጣኔ መሰረት ሆነን እንታያለን።
ሌላው ሐበሻ ሴሜቲክ ናቸው እንጂ ኩሸቲክ አይደሉም ይሉናል። ከመነሻው እንዳየነው ሴም ለኩሽ አጎቱ ነው የኩሽ አባት እና ሴም ወንድማማቾች ናቸው ማለት ነው። በቃ የኛ አመጣጥ እዚህ ጋር በአራት ነጥብ ተዘግቷል። ኩሸቲክ እና ሴመቲክ የአንድ ዘር ልጆች ነን። ታዲያ ሐበሻ የሚለው ቃል የመጣው ከየት ነው? ከተባለ መልሱ ከአረቦች ነው።
ነብዩ መሃመድ ከቆሬሾች ጋር ከፍተኛ ችግር ውስጥ በነበረበት ወቅት በጃፋር መሪነት የነብዩ የቅርብ ሰዎች የነበሩትን ወደ ኢትዮጵያ ሲልኩ የተናገሩትን ቃል እጠቅሳለው ቃሉ ቃል በቃል ከቁርአን ነው የተወሰደው << ሐበሻ (ኢትዮጵያ) የእውነት አገር ናት በውስጧም ሰውን የማይበድል እርሱም ዘንድ አንድም የማይበደል ንጉስ አለና ወደዚያ ብትሄዱ መልካም ነው>> ይላል። ነብዩ መሃመድ በእስልምና እምነት አማኞች ዘንድ ትልቅ ቦታ ያላቸው ሰው ናቸው። ሐበሻ የሚለውን ስም እስካሁንም ድረስ አረቦች ይጠቀሙበታል። ታዲያ በነብዩ መሃመድ እንዲህ የተገለጹት ደግ በደልን የማያደርጉ ህዝብን የማይበድሉ መሪ ኢትዮጵያ ነበራት። እኚህ መሪ የሴምም የኩሽም ልጅ የሴምና የኩሽ ሃረግ የነበራቸው መሪ ናቸው እንጂ ዛሬ ዛሬ እንደሚነገረው የወያኔ ፖለቲካ እና የወያኔ አካሄድ የሚከተሉ እንደሚሉት ሐበሻ ስለተባሉ የሴም ወገን ናቸው ተብሎ መነገሩ የራስን ታሪክ ጠንቅቆ ካለመረዳት እና የፖለቲካን ትርፍ ለማግኘት ተብሎ ታሪክን በገዛ ፍቃድ እንደመጣል ይቆጠራል። ለኢትዮጵያ የሚሰጥ የታሪክ፣ የጀግንነት፣ የስልጣኔ፣ የሃይማኖት፣ የስነ ፈጠራ፣ የባህል፣ የቋንቋ፣ ድርሻ የሴምም የኩሽም እኩል ታሪክ ነው። ማንም ከማንም የተነጠለ ታሪክ የለንም። ማንም ከማንም የሚለያይ ስራም የለንም። ወያኔ ለአገዛዙ ማቆያ ለስልጣኑም ማራዘሚያ በማሰብ መጀመሪያ እና መሃል የሌለው ጫፍ ብቻ ያለው ታሪክ ይነግረናል። ጫፉ ላይ ወጥተን ከማንነታችን ውጪ ግዜአዊ የፖለቲካ ትርፍ ፍለጋ ማንነታችንን እና አገራችንን አደጋ ላይ መጣል ተገቢ አይደለም ነገም ታሪክ ይጠይቀናል ማንም ከተጠያቂነት አያመልጥም። ስለዚህ ወደ እውነተኛው ማንነታችን መመለስ ያስፈልገናል።
እንደ ማሳሰቢያ መናገር የምፈልገው አንድ ሰው የተለየ ሃሳብ ለምን አመጣ ተብሎ አይከለከልም ማንም የፈለገውን ሃሳብ ማምጣት ይችላል ያንን ሃሳብ ግን በማስረጃ ሊያቀርብ ያስፈልጋል። በነጻ ሚዲያ ዘርፍ የተሰማራችሁ ጋዜጠኞች በታሪክ ዙሪያ የተለየ ሃሳብ ያለው ሰው ካለ ወደሚዲያው በመጋበዝ ከታሪክ ሙሁራኑ ጋር ግልጽ ትንታኔ ከሁለቱም ወገን እንዲሰጡበት በማድረግ እና ጥያቄአቸውን በማስረጃ እንዲመልሱ በማድረግ እውነታውን ህዝቡ እንዲያውቀው የማድረጉን ስራ ቢሰራ በህዝቡ ዘንድ የሚኖሩትን ብዥታዎች ያጠራዋል። ህዝብን በመከፋፈል ዙሪያ ወያኔ የሚጠቀምበትን መንገድ አንድ አንዶችም በመከተል ላይ ስለሆኑ የፈረሰውን በመገንባት የሃሰት ታሪካዊ ወሬዎችን እውነተኛ በሆነው ታሪክ በማነጽ ያስፈልጋል። ጥያቄ አንሺውን እና ሙሁራኑን በማገናኘት በየግዜው ትንታኔ እንዲሰጥበት በማድረግ በጋዜጠኝነት ሙያውስጥ ያላችሁ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ለአገራችሁ ታሪክ ስሩ። ኢትዮጵያን ወደ ሰላሟ እና ወደ እረፍቷ የሚያመጣት መልካም መንገድ ነውና።
ከተማ ዋቅጅራ
በኢትዮጵያ ህዝቡ የመንቀሳቀስ ነፃነቱ ጠብመንጃ በታጠቁ የአገዛዙ ቡድኖች መገፈፉ ታወቀ፡፡
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም ደግሞ በሰሜኑ ክፍል እንደልብ ከቦታ ቦታ መዘዋወር እጅግ በጣም ከባድ እየሆነ እንደመጣና ህዝቡ የመንቀሳቀስ ነፃነቱ ጠብመንጃ በታጠቁ የአገዛዙ ቡድኖች መገፈፉ ታወቀ፡፡
በእጅጉ እየተፋፋመ ከሚገኘው ባንዳነትን በአርበኝነት ከማስወገድ የመሳሪያ ትግል ጋር በተያያዘ ህወሓት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ባሰማራቸው ክፍተኛ ቁጥር ያላቸው ፌደራል ፖሊስ፣ ልዩ ኃይል እና መከላከያ ሰራዊት ጦር እንዲሁም ደህንነቶቹ በየጥቂት ኪሎ ሜትሮች የርቀት ልዩነት ቁጥር ስፍር የሌላቸው የፍተሻ ኬላዎችን በማቋቋም ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሱ ሰላማዊ ዜጎችን በብርበራ ስም ክፉኛ እያዋከበ፣ እያሸማቀቀና እያሸበረ ይገኛል፡፡
...
ኢትዮጵያ ውስጥ በተለይም ደግሞ በሰሜኑ ክፍል እንደልብ ከቦታ ቦታ መዘዋወር እጅግ በጣም ከባድ እየሆነ እንደመጣና ህዝቡ የመንቀሳቀስ ነፃነቱ ጠብመንጃ በታጠቁ የአገዛዙ ቡድኖች መገፈፉ ታወቀ፡፡
በእጅጉ እየተፋፋመ ከሚገኘው ባንዳነትን በአርበኝነት ከማስወገድ የመሳሪያ ትግል ጋር በተያያዘ ህወሓት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል ባሰማራቸው ክፍተኛ ቁጥር ያላቸው ፌደራል ፖሊስ፣ ልዩ ኃይል እና መከላከያ ሰራዊት ጦር እንዲሁም ደህንነቶቹ በየጥቂት ኪሎ ሜትሮች የርቀት ልዩነት ቁጥር ስፍር የሌላቸው የፍተሻ ኬላዎችን በማቋቋም ከቦታ ቦታ የሚንቀሳቀሱ ሰላማዊ ዜጎችን በብርበራ ስም ክፉኛ እያዋከበ፣ እያሸማቀቀና እያሸበረ ይገኛል፡፡
...
ከአዲስ አበባ ወደ ጎንደርና ከአዲስ አበባ ወደ ወሎ በሚወስዱ ጎዳናዎች ላይ የፍተሻ ኬላዎች በከፍተኛ ሁኔታ ተጠናክረው የመንገደኞችን ሰብዓዊ መብት በረገጠ መልኩ ብርበራ፣ ማዋከብና ማሸብር እየተፈፀመ ይገኛል፡፡ ከአዲስ አበባ ደሴ በተዘረጋው መስመር በቅርቡ በተጀመረው ከዚህቀደም ታይቶ የማያውቅና ያልተለመደ ጥብቅ ጥበቃ፣ ቁጥጥር፣ ብርበራና በጦር መሳሪያ ማስፈራራት ጋር በተያያዘ ህዝቡ የአርበኞች ግንቦት 7 ታጋዮች በአካባቢው ገብተዋል በሚል ግምት የትግል መንፈሱ እንደተነሳሳ እና የተሰማውን ከፍተኛ ደስታ ውስጥ ለውስጥ እየገለፀ እንደሆነ ምንጮቻችን ተናግረዋል፡፡
በተለይም ደግሞ ከጎንደር ሁመራና ከጎንደር መተማ በሚደረጉ ጉዞዎች ላይ ገደብ የሌለው ቁጥጥር ስለሚደረግ ህዝቡ በተለይም ደግሞ ወጣቶች ፈፅሞ በነፃነት መንቀሳቀስ ከማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል፡፡ ከጎንደር ወደ አርማጭሆ፣ ወልቃይት፣ ጠገዴና መተማ ለስራ የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች አርበኞች ግንቦት 7ን ለመቀላቀል እየተጓዛችሁ ነው በሚል በየቀኑ በገፍ እየታፈኑ ወደ ወህኒ በመጋዝ ላይ ናቸው፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ የህወሓት አገዛዝ የተለያዩ ወንጀሎችን ራሱ በማቀነባበር ደጋፊዎቹ ያልሆኑ መንገደኞችንና አሽከርካሪዎችን ወንጀል ሲሰሩ እጅ ከፍንጅ እንደያዛቸው በማስመሰል በቁጥጥር ስር አውሎ በሃሰት እያሰራቸው ነው፡፡ የህወሓት ደህንነቶች ከጭልጋ ወደ ጯሂትና ደልጊ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚመላለሱ የህዝብ መጓጓዣ ሚኒባሶች ላይ የጦር መሳሪያዎችን በስውር እየጫኑ ማጥቃት የሚፈልጉትን ግለሰብ ጠብቀው አሳበው በቁጥጥር ስር እያዋሉ እንደሆነ በተደጋጋሚ ከቦታው እየደረሱን የሚገኙት መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከሰሞኑ የህወሓት ደህንነቶች የሰሌዳ ቁጥር 11243 የሆነች ሚኒባስ ላይ ወደ አስር የሚጠጉ ክላሽን ኮቮችን በድብቅ በማስጫን ሚኒባሷን ከጭልጋ ደልጊና ጯሂት በሚወስደው መስመር ከምትገኘው ብሆና ላይ ጠብቀው በቁጥጥር ስር በማዋል ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሊበቀሉት በሚፈልጉት ሰው ላይ እርምጃ ወስደዋል፡፡
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
በተለይም ደግሞ ከጎንደር ሁመራና ከጎንደር መተማ በሚደረጉ ጉዞዎች ላይ ገደብ የሌለው ቁጥጥር ስለሚደረግ ህዝቡ በተለይም ደግሞ ወጣቶች ፈፅሞ በነፃነት መንቀሳቀስ ከማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል፡፡ ከጎንደር ወደ አርማጭሆ፣ ወልቃይት፣ ጠገዴና መተማ ለስራ የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች አርበኞች ግንቦት 7ን ለመቀላቀል እየተጓዛችሁ ነው በሚል በየቀኑ በገፍ እየታፈኑ ወደ ወህኒ በመጋዝ ላይ ናቸው፡፡
ከዚህ ጋር በተያያዘ የህወሓት አገዛዝ የተለያዩ ወንጀሎችን ራሱ በማቀነባበር ደጋፊዎቹ ያልሆኑ መንገደኞችንና አሽከርካሪዎችን ወንጀል ሲሰሩ እጅ ከፍንጅ እንደያዛቸው በማስመሰል በቁጥጥር ስር አውሎ በሃሰት እያሰራቸው ነው፡፡ የህወሓት ደህንነቶች ከጭልጋ ወደ ጯሂትና ደልጊ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚመላለሱ የህዝብ መጓጓዣ ሚኒባሶች ላይ የጦር መሳሪያዎችን በስውር እየጫኑ ማጥቃት የሚፈልጉትን ግለሰብ ጠብቀው አሳበው በቁጥጥር ስር እያዋሉ እንደሆነ በተደጋጋሚ ከቦታው እየደረሱን የሚገኙት መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ ከሰሞኑ የህወሓት ደህንነቶች የሰሌዳ ቁጥር 11243 የሆነች ሚኒባስ ላይ ወደ አስር የሚጠጉ ክላሽን ኮቮችን በድብቅ በማስጫን ሚኒባሷን ከጭልጋ ደልጊና ጯሂት በሚወስደው መስመር ከምትገኘው ብሆና ላይ ጠብቀው በቁጥጥር ስር በማዋል ከተሳፋሪዎቹ መካከል ሊበቀሉት በሚፈልጉት ሰው ላይ እርምጃ ወስደዋል፡፡
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
ወያኔ ሰራሽ የርስበርስ ግጭት ደግሶችን እናምክን!!!
ወያኔ ሰራሽ የርስበርስ ግጭት ደግሶችን እናምክን!!!
==============================
Nov 27, 2015 Editorial
==============================
Nov 27, 2015 Editorial
የወያኔ ስርዓት ኢትዮጵያ የተዋቀረችው በህዝብ ታሪካዊ አብሮነትና ተዛምዶ ላይ ሳይሆን የብሔር ብሔረሰብ ልዩነቶችን በማጥበቅና ልዩነትንም የርስበርስ ጥርጣሬና ግጭት ምንጭ እንዲሆን በማለም ነው። ልዩነት የግጭትና የጠብ ምንጭ እንዲሆን ተደርጎ ነው የተዋቀረውና ብፖለቲካ ደረጃ የተገፋው። አንዱ ብሔረሰብ ሌላው ብሔረሰብ ክልል ውስጥ ሲሆን ባዕድነት እንዲሰማውና እንዲሰጋ አንዱ አንዱን በጥርጣሬ እንዲመለከተው ተደርጎ ነው ሀያ አራት አመት ሙሉ የተገፋውና እየተገፋ ያለው።
ይህም ሆኖ በዘመነ ወያኔ በየቦታው የተከሰቱ የብሔር ሌብሔርሰብ ግጭቶች በሙሉ የተቀሰቀሱት በራሱ በመንግስት ባለስልጣኖች እንጂ መቼም ህዝብ ለሕዝብ ሆኖ አያውቅም። በተለያዩ የደቡብ የሀገሪቱ ክፍሎች አማሮችን ኢሰብዓዊ በሆነ መንገድ ለማባረር የተወሰዱት ርምጃዎች ራሳቸው ሰለባዎቹ እንደሚናገሩት ለስቃይ የዳረጋቸው ነዋሪው ሕዝብ ሳይሆን ባለስልጣናቱ መሆናቸውን በግልጽ ሲናገሩ ሰምተናል።
በቤኒሻጉልና ጉሙዝ ክልል ውስጥ ሰሞኑን ይፋ መሆኑ የተነገረው በአስቃቂ ሁኔታ ተገድለው ተቀብረው የተገኙ አማሮች አስከሬን መገኘቱ ታውቋል። ይህም ወያኔ ባስለጠናቸውና ባዘዛቸው ካድሬዎችና ባለስልጣኖች የተከወነ እንጂ በሕዝብ ተነሳሽነት የተፈጸመ አለመሆኑ የታወቀ ነው። ቀደም ሲል በመንግስት ደረጃ የተቀነባበረ አማሮችን የማፈናቀል ዘመቻ ተከታይ ስራ መሆኑን ለማወቅ ብዙ አዳጋች አይደለም። በወገኖቻችን ላይ በሚዘገንን መንገድ የተፈጸመው ግፍ ዘልቆ ይሰማናል:: ሊሰማንም የገባል። ቁጭታችንና ሀዘናችን ግን ወያኔ ወደሚፈልገው የሕዝብ ለሕዝብ ግጭት ምክንያት እንዳይሆን ከፍተኛ ትዕግስትና ጥንቃቄ ልናደርግ ይገባል።
ሰሞኑን በታሪክ ሊዘገብ ከሚችል ልዩነት ውጭ ባኗኗር በባህልና ቋንቋ የማይለያዩትን የሰሜን ኢትዮጵያ ህዝቦች ቅማንትና አማራ በሚል ለማጋጨት ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛል። ይህ ሰይጣናዊ አካሔድ በወያኔ የፖለቲካ ተንኮል እየተመራ እንዳለ የሚያሳዩ ብዙ መረጃዎች አሉ። የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦች ሁሉም ካላንዳች መድሎና ልዩነት ሀገሪቱ ላይ መብታቸው ተጠብቆ እንዲኖሩ ሁሉም በየበኩላቸው የሚያደርጉትን ጥረትና ትግል እንደግፋለን። በህዝባችን መካከል ያሉት ግንኙነቶች ሊሆን የሚችለው እንዱ አንዱን የማገዝ እንጂ ርስበርስ የመጋጨትም ሆነ የመናቆር አይደለም።
ኢትዮጵያውያን ብሄርና ዘር ሳንለይ ይህንን የወያኔ ተንኮል ችግሩ ወደባሰ ደረጃ ሳይሄድ መቋቋምና ማክሸፍ ይጠበቅብናል። ይህ ታሪክነታችንና ታላቅ ሕዝብነታችንን የማይመጥን አሳፋሪ የወያኔ ፖለቲካ እንደሀገር እንዳያጠፋን ሁላችንም በንቃትና በቁርጠኝነት መቋቋም ይኖርብናል።
አርበኞች ግንቦት ፯ ልዩነት ጌጥ እንጂ የጠብና የግጭት ምክንያት የማይሆንባት ሀገር ፥ የየብሔረሰቡ መብት ሁሉ የይስሙላ ሳይሆን በተግባር የተረጋገጠባት ሀገር ፥ ከነልዩነታችን በጋራ ራዕይ የምንተሳሰርባትና የምንገነባት ሀገር እንድትኖረን የሚያደርገውን ትግል ይቀጥላል። የቻልክ በአካል ተቀላቀለን። ያልቻልክ በያለህበት የወያኔ ዘራፊዎች ያሰቡትን የተንኮል ጉንጉን በመበጣጠስ ተሳተፍ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!
Wednesday, 25 November 2015
ሱዳንን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስነው የድንበር ሊካለል ነው ተባለ
ሱዳንን ከኢትዮጵያ ጋር የሚያዋስነው የድንበር ሊካለል ነው ተባለ።
በታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ የድንበር ማካለሉ ስራ ሙሉ በሙሉ እንደሚከናወን ባለፈው አመት መጨረሻ አለያም በዚህ አመት መጀመሪያ አካባቢ ተካሂዶ በነበረው የአልበሽር በአለ ሲመት ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ለሱዳን ባለስልጣናት ማረጋገጫ ሰጥተው እንደተመለሱ በጊዜው በደረሰን መረጃ መሠረት እዚሁ ፌስ ቡክ ላይ አሳውቀን ነበር ። አሁን ሱዳን ትሪቡን እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ የድንበር ማካለሉ ስራ በሚቀጥለው ወር ውስጥ እንደሚከናወን ገልፆ በዚሁ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር የሱዳኑ ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት አዲስ አበባ መግባታቸውን ገልጿል። ከኤርትራ እስከ ደቡብ ሱዳን ድንበር ድረስ 1600 ኪሎ ሜት ርዝመት ባለውና ወደ ኢትዮጵያ ከ40 ኪሎ ሜትር በላይ ዘልቆ ወደ ውስጥ የሚገባው የሱዳን የድንበር ይገባኛል ጥያቄ አብዛኛውን የሀገሪቱን ለም መሬት በስፋት ለሱዳን የሚሰጠውና ከዚህ ወር መጠናቀቅ በሗላ የሚተገበረው ስምምነት ከኢትዮጵያ ህዝብ እውቅናና ይሁንታ ውጪ በህውሃት/ኢሕአዴግ ጁንታ ባለስልጠናት ውሳኔ የሚተገበር ነው። ይህ የድንበር ማካለል በትግበራ ላይ ከዋለ በህውሃት የአገዛዝ ዘመን ከተፈፀሙና ታሪክ ከማይዘነጋቸው በርካታ ስህተቶች መካከል አሰብ ለኤርትራ ከተሰጠበት መራር እውነት ቀጥሎ በጥቁር ቀለም የቀለመ ሁለተኛው ግዙፍ ስህተት ሆኖ ይመዘገባል፡፡
በታህሳስ ወር መጀመሪያ ላይ የድንበር ማካለሉ ስራ ሙሉ በሙሉ እንደሚከናወን ባለፈው አመት መጨረሻ አለያም በዚህ አመት መጀመሪያ አካባቢ ተካሂዶ በነበረው የአልበሽር በአለ ሲመት ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ ለሱዳን ባለስልጣናት ማረጋገጫ ሰጥተው እንደተመለሱ በጊዜው በደረሰን መረጃ መሠረት እዚሁ ፌስ ቡክ ላይ አሳውቀን ነበር ። አሁን ሱዳን ትሪቡን እንደዘገበው ከሆነ ደግሞ የድንበር ማካለሉ ስራ በሚቀጥለው ወር ውስጥ እንደሚከናወን ገልፆ በዚሁ ጉዳይ ላይ ለመነጋገር የሱዳኑ ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት አዲስ አበባ መግባታቸውን ገልጿል። ከኤርትራ እስከ ደቡብ ሱዳን ድንበር ድረስ 1600 ኪሎ ሜት ርዝመት ባለውና ወደ ኢትዮጵያ ከ40 ኪሎ ሜትር በላይ ዘልቆ ወደ ውስጥ የሚገባው የሱዳን የድንበር ይገባኛል ጥያቄ አብዛኛውን የሀገሪቱን ለም መሬት በስፋት ለሱዳን የሚሰጠውና ከዚህ ወር መጠናቀቅ በሗላ የሚተገበረው ስምምነት ከኢትዮጵያ ህዝብ እውቅናና ይሁንታ ውጪ በህውሃት/ኢሕአዴግ ጁንታ ባለስልጠናት ውሳኔ የሚተገበር ነው። ይህ የድንበር ማካለል በትግበራ ላይ ከዋለ በህውሃት የአገዛዝ ዘመን ከተፈፀሙና ታሪክ ከማይዘነጋቸው በርካታ ስህተቶች መካከል አሰብ ለኤርትራ ከተሰጠበት መራር እውነት ቀጥሎ በጥቁር ቀለም የቀለመ ሁለተኛው ግዙፍ ስህተት ሆኖ ይመዘገባል፡፡
ሕወሓት መራር የሽንፈት ፅዋን ዳግም ተጎነጨ!!
ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋንና ድርጅታቸው አርበኞች ግንቦት 7 ‘’በአሸባሪነት’’ እንዲፈረጅላቸው ሌት ተቀን የአውሮጳ ህብረትን ሲማፀኑ የነበሩት ሕወሓቶች ዳግም የሽንፈት ፅዋን ተጎነጩ። የአውሮጳ ህብረት አርበኛው ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋን በመጭው ማክሰኞ (Dec 1) በአውሮጳ መዲና በብራስልስ ''ድርቅና ረሀብ በኢትዮጵያ'' በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ህዝባዊ ውይይት ንግግር እንዲያደርጉ በክብር በመጋበዝ ህብረቱ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ያለውን ድጋፍና አጋርነት ከማሳየቱም ባሻገር በኢትዮጵያ አሸባሪው ማን እንደሆነ ጠቁሞ አልፏል።
እንግዲህ በሕወሓት ካምፕ እንቅል የሚባል ነገር አይታሰብም!! አሸባሪው ማን እንደሆነ በአውሮጳ ህብረት ዘንድ በግልጽ ተለይቷልና!!
ለማነኛውም እንዳያመልጣችሁ!!!
ከአርበኛው ፕሮፌሰር ብርሀኑ ነጋ ቆራጥ አመራር ጋር ወደፊት!!!
Wednesday, 18 November 2015
“15 ሚሊዮን ህዝብ መደበቅ ሰማይን በመዳፍ ለመሸሸግ እንደ መሞከር ይቆጠራል” (በውቀቱ ስዩም)

“ገጽታ ግንባታ?”
በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን የፍርድ ምኒስተር የነበሩት ኣፈንጉስ ነሲቡ የሌባ ብዛት ቢያስቸግራቸው ኣንድ መላ መቱ፡፡ ሲሰርቅ የተገኘ ወሮበላ ግንባሩ ላይ በጋለ ስለት ምልክት እንዲደረግበት ደነገጉ፡፡ ታድያ ሌቦች የዋዛ ስላልነበሩ ሻሽ በመጠምጠም የግንባራቸውን ጠባሳ ሊሰውሩት ሞክረዋል፡፡ በጊዜው ደግሞ ሻሽ መጠምጠም ካክሱም ዘመነ መንግስት ጀምሮ የወረደ የነገስታቱና የመሳፍንቱ ወግ ነበር፡፡ ጮሌ ሌቦች ውርደታቸውን ከመሸፈን ኣልፈው የንጉስ ገጽታ ተላብሰው ብቅ ኣሉ፡፡
በዘመናችን የተራቡ ዜጎችን መደበቅ እንደ ገጽታ ግንባታ የሚቆጥሩ ሰዎችን ከባለሻሽ ሌቦች ለይቼ ኣላያቸውም፡፡
በነገራችን ላይ፤ ብርቱካን ኣሊ ግለሂስ ያደረገችበትን ዘገባ ካየሁ በኋላ ለጊዜው ለመናደድ እንኳ ቸግሮኝ ነበር፡፡ ዘገባውን የሠራው ጋዜጠኛ እንዲህ ኣይነቱን ካንድ ድንጋይ የተጠረበ ደደብነት ተሸክሞ የመኖር ችሎታው በጣም ኣስደነቀኝ፡፡ በዚህ በሰላቢው ቀን ይቅርና፤ በደህናው ቀን እንኳ የባላገሩን ራብና መከራ ከጉያው የበቀልን ልጆቹ እናውቀዋለን ፡፡ ኣስራ ኣምስት ሚሊዮን ህዝብ መደበቅ ሰማይን በመዳፍ ለመሸሸግ እንደ መሞከር ይቆጠራል፡፡ መመፍትሄው በተቸገሩ ሰዎች ጫማ ቆሞ ነገሮችን መመልከት ነው፡፡ ለነገሩ ችግርን ያልቀመሰ ሰው ለችግረኛ መራራት እንዴት ይቻለዋል?
ኣብን ተውትና ፤ንገሩት ለወልድ
ተገርፏል ተሰቅሏል ፤ እሱ ያውቃል ፍርድ
እንዲል ባላገር፡፡
ተገርፏል ተሰቅሏል ፤ እሱ ያውቃል ፍርድ
ሰማያዊ ፓርቲ ያቀደውን ህዝባዊ ስብሰባ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር መገደዱን ገለፀ
ሰማያዊ ፓርቲ ያቀደውን ህዝባዊ ስብሰባ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር መገደዱን ገለፀ
• ‹‹ከደህንነትና ፖሊሶች ጋር ካልተነጋገርኩ አልፈቅድም›› አስተዳደሩ
• ‹‹ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት እነሱን መለማመጥ አያስፈልግም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
ከአባላቱና ደጋፊዎቹ ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ጋር ለመነጋገር ህዳር 18/2008 ዓ.ም ህዝባዊ ስብሰባ ለማድረግ አቅዶ የነበረው ሰማያዊ ፓርቲ የአዲስ አበባ አስተዳደር በፈጠረበት መሰናክል ምክንያት ያቀደውን ህዝባዊ ስብሰባ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር መገደዱን ሊቀመንበሩ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ባስገባው የእውቅና ደብዳቤ ላይ ‹‹ህዳር 18 አልፏል፡፡ ይቀመጥ!›› ብሎ መርቶበት የነበረው አስተዳደሩ ፓርቲው ‹‹ህዳር 18 አላለፈም›› ባለው መሰረት ‹‹በስህተት ነው፡፡ ሰኞ ኑ!›...› ብሎ ሰኞ ህዳር 6/2008 ዓ.ም ተቀጥረው እንደነበር እና ወደ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል መመራቱን ተገልጾላቸው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ሰኞ ሲሄዱ ‹‹ዛሬ አይመችም፣ ነገ ኑ›› ተብሎ ለረቡዕ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ዛሬ ህዳር 8/2008 ዓ.ም በቀጠሯቸው መሰረት ከህዳር 6 ጀምሮ ለ3ኛ ጊዜ፤ እውቅናውን ከጠየቀ በኋላ በአጠቃላይ ደግሞ ለ8ኛ ጊዜ ሲሄዱ የስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ‹‹ከደህነትና ፖሊስ ጋር እየተማከርኩ ነው፡፡ ከእነሱ ጋር ሳልማከር አልፈቅድም›› ብሎ እንደመለሳቸው ገልጸዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ለአስተዳደሩ ደብዳቤ መፃፍ ከጀመረ 15 ቀናት ያለፉት ሲሆን ለ6ኛ ጊዜ ደብዳቤውን ማስገባቱ ይታወቃል፡፡ አስተዳደሩ የሰላማዊ ሰልፍ ወይም የስብሰባ እውቅናን መከልከል እንደማይችል፣ ነገር ግን የደህንነት አሊያም የቦታ ችግር ካለ ቦታ ወይንም ጊዜ ሊቀይር ብቻ እንደሚችል የገለፁት ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በተደጋጋሚ ለአስተዳደሩ ደብዳቤ ለማስገባት የተገደዱት የአዳራሽ ኪራይ ለመክፈል አስደዳደሩ እውቅና ስለሚያስፈልግ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡
ይሁንና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ለአስተዳደሩ አሳውቆ በ48 ሰዓት ውስጥ መልስ ካልሰጠ እውቅና እንደሰጠ ስለሚቆጠርና የአስተዳደሩን መሰናክልም ስለሚቀንሰው ስብሰባውን ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ‹‹መስተዳደሩ እንዲህ የሚጠመው የስብሰባ አዳራሽ እንዳናገኝ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ከሆነ ግን እነሱን ይህን ያህል መለማመጥ አያስፈልግም፡፡ በመሆኑም እንደተለመደው የወሰዱትን እርምጃ ቢወስዱም ስብሰባውን ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር እየተገደድን ነው›› ብለዋል፡፡
• ‹‹ከደህንነትና ፖሊሶች ጋር ካልተነጋገርኩ አልፈቅድም›› አስተዳደሩ
• ‹‹ሰላማዊ ሰልፍ ለመጥራት እነሱን መለማመጥ አያስፈልግም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
ከአባላቱና ደጋፊዎቹ ጋር በወቅታዊ ጉዳዮች ጋር ለመነጋገር ህዳር 18/2008 ዓ.ም ህዝባዊ ስብሰባ ለማድረግ አቅዶ የነበረው ሰማያዊ ፓርቲ የአዲስ አበባ አስተዳደር በፈጠረበት መሰናክል ምክንያት ያቀደውን ህዝባዊ ስብሰባ ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር መገደዱን ሊቀመንበሩ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ባስገባው የእውቅና ደብዳቤ ላይ ‹‹ህዳር 18 አልፏል፡፡ ይቀመጥ!›› ብሎ መርቶበት የነበረው አስተዳደሩ ፓርቲው ‹‹ህዳር 18 አላለፈም›› ባለው መሰረት ‹‹በስህተት ነው፡፡ ሰኞ ኑ!›...› ብሎ ሰኞ ህዳር 6/2008 ዓ.ም ተቀጥረው እንደነበር እና ወደ ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል መመራቱን ተገልጾላቸው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ሰኞ ሲሄዱ ‹‹ዛሬ አይመችም፣ ነገ ኑ›› ተብሎ ለረቡዕ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ዛሬ ህዳር 8/2008 ዓ.ም በቀጠሯቸው መሰረት ከህዳር 6 ጀምሮ ለ3ኛ ጊዜ፤ እውቅናውን ከጠየቀ በኋላ በአጠቃላይ ደግሞ ለ8ኛ ጊዜ ሲሄዱ የስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ‹‹ከደህነትና ፖሊስ ጋር እየተማከርኩ ነው፡፡ ከእነሱ ጋር ሳልማከር አልፈቅድም›› ብሎ እንደመለሳቸው ገልጸዋል፡፡
ሰማያዊ ፓርቲ ለአስተዳደሩ ደብዳቤ መፃፍ ከጀመረ 15 ቀናት ያለፉት ሲሆን ለ6ኛ ጊዜ ደብዳቤውን ማስገባቱ ይታወቃል፡፡ አስተዳደሩ የሰላማዊ ሰልፍ ወይም የስብሰባ እውቅናን መከልከል እንደማይችል፣ ነገር ግን የደህንነት አሊያም የቦታ ችግር ካለ ቦታ ወይንም ጊዜ ሊቀይር ብቻ እንደሚችል የገለፁት ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በተደጋጋሚ ለአስተዳደሩ ደብዳቤ ለማስገባት የተገደዱት የአዳራሽ ኪራይ ለመክፈል አስደዳደሩ እውቅና ስለሚያስፈልግ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡
ይሁንና ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ለአስተዳደሩ አሳውቆ በ48 ሰዓት ውስጥ መልስ ካልሰጠ እውቅና እንደሰጠ ስለሚቆጠርና የአስተዳደሩን መሰናክልም ስለሚቀንሰው ስብሰባውን ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር እየተገደዱ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልፀዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ‹‹መስተዳደሩ እንዲህ የሚጠመው የስብሰባ አዳራሽ እንዳናገኝ ነው፡፡ ሰላማዊ ሰልፍ ከሆነ ግን እነሱን ይህን ያህል መለማመጥ አያስፈልግም፡፡ በመሆኑም እንደተለመደው የወሰዱትን እርምጃ ቢወስዱም ስብሰባውን ወደ ሰላማዊ ሰልፍ ለመቀየር እየተገደድን ነው›› ብለዋል፡፡
እነ ማቲያስ መኩሪያ ጥፋተኛ ተባሉ
እነ ማቲያስ መኩሪያ ጥፋተኛ ተባሉ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
አይ ኤስ በኢትዮጵውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ድርጊት ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰበብ የታሰሩት ማቲያስ መኩሪያ፣ ብሌን መስፍን፣ ተዋቸው ዳምጤ እና መሳይ ደጉሰው ዛሬ ህዳር 8/2008 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በመናገሻ ምድብ ችሎት ቀርበው ጥፋተኛ ተብለዋል፡፡
ችሎቱ በቢሮ ከመታየቱም ባሻገር ችሎት አስከባሪው ‹‹መግባት አይቻልም፡፡ ተከልክሏል፡፡ የከለከልኩት ግን እኔ አይደለሁም፡፡›› በማለቱ ማንም እንዳይገባ ተከልክሎ በዝግ ታይቷል፡፡ ፖሊስ ተከሳሾቹ ላይ የቪዲዮ ማስረጃ አለኝ በማለቱ ተከሳሾቹም ‹‹የቪዲዮ ማስረጃው ለእኛም በመከላከያ ማስረጃነት ስለሚያገለግለን ይቅረብልን›› ባሉት መሰረት ቪዲዮውን አይቶ ብይን ለመስጠት ለወራት ሲቀጠርባቸው ቆይቷል፡፡
ከመሳይ ደጉሰው ውጭ ያሉት ተከሳሾች የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ ተከሳሾቹ ከታሰሩ ከ6 ወር በላይ የሆናቸው ሲሆን በፍርድ ሂደቱ ከፍተኛ መጉላላት እየደረሰባቸው እንደሆነ በተደጋጋሚ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡ እነ ማቲያስን ጥፋተኛ ያለው ፍርድ ቤቱ ለህዳር 22/2008 ዓ.ም ለውሳኔ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
አይ ኤስ በኢትዮጵውያን ላይ የፈፀመውን አሰቃቂ ድርጊት ለመቃወም መንግስት በጠራው ሰልፍ ሰበብ የታሰሩት ማቲያስ መኩሪያ፣ ብሌን መስፍን፣ ተዋቸው ዳምጤ እና መሳይ ደጉሰው ዛሬ ህዳር 8/2008 ዓ.ም በፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በመናገሻ ምድብ ችሎት ቀርበው ጥፋተኛ ተብለዋል፡፡
ችሎቱ በቢሮ ከመታየቱም ባሻገር ችሎት አስከባሪው ‹‹መግባት አይቻልም፡፡ ተከልክሏል፡፡ የከለከልኩት ግን እኔ አይደለሁም፡፡›› በማለቱ ማንም እንዳይገባ ተከልክሎ በዝግ ታይቷል፡፡ ፖሊስ ተከሳሾቹ ላይ የቪዲዮ ማስረጃ አለኝ በማለቱ ተከሳሾቹም ‹‹የቪዲዮ ማስረጃው ለእኛም በመከላከያ ማስረጃነት ስለሚያገለግለን ይቅረብልን›› ባሉት መሰረት ቪዲዮውን አይቶ ብይን ለመስጠት ለወራት ሲቀጠርባቸው ቆይቷል፡፡
ከመሳይ ደጉሰው ውጭ ያሉት ተከሳሾች የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ ተከሳሾቹ ከታሰሩ ከ6 ወር በላይ የሆናቸው ሲሆን በፍርድ ሂደቱ ከፍተኛ መጉላላት እየደረሰባቸው እንደሆነ በተደጋጋሚ ለፍርድ ቤቱ አቤቱታ ሲያቀርቡ ቆይተዋል፡፡ እነ ማቲያስን ጥፋተኛ ያለው ፍርድ ቤቱ ለህዳር 22/2008 ዓ.ም ለውሳኔ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
የወልቃይት ህዝብ ለነፃነቱ ሊታገል ከመቸውም ጊዜ በላይ ቆርጦ በአንድነት መነሳቱ ታወቀ
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ)
የወልቃይት ህዝብ ለነፃነቱ ሊታገል ከመቸውም ጊዜ በላይ ቆርጦ በአንድነት መነሳቱ ታወቀ፡፡
====================================================
የወልቃይት ህዝብ ህወሓት ገና ከሽፍትነቱ ጀምሮ ተደጋጋሚ ግፍና በደል ያደረሰበት በመሆኑ መቸም የማይፈታ ቂም አለው፡፡ ህወሓት ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ ደግሞ ሳይፈልግ ከጎንደር እንዲገነጠል ተደርጎ ወደ ትግራይ ክልል በመጠቃለሉ ሲያነሳው የቆየው ያልተመለሰ ጥያቄ አለው፡፡
ህወሓት የወልቃይት ህዝብ ያነሳውን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የጀመረውን የነፃነት ትግል እንቅስቃሴ ጦር ኃይሉን ተጠቅሞ ለመደፍጠጥ ወደ አካባቢው ያለማቋረጥ ሰራዊት እያዘመተ አሰቃቂ የህዝብ ጭፍጨፋ በማድረግ ዘር ማጥፋት ፈፅሟል፡፡...
ሆኖም ህወሓት የወልቃይትን ህዝብ በጥይት በመግደል ዝም ማሰኘት ሳይችል ቀርቶ ዛሬ የበለጠ ተደራጅቶበት ጠብመንጃውን ወልውሎ በአንድነት ተነስቷል፡፡ ወደ በረሃ እየወረደ አርቨኞች ግንቦት 7 እያፋፋመው የሚገኘውን አርበኝነት የሚቀላቀለውም ከዕለት ዕለት ቁጥሩ በእጅጉ አይሏል፡፡
ከሰሞኑ ደግሞ የወልቃይት ሰው ማር ዘነብ ልዩ ቦታው ቴፍ ላይ በመሰባሰብ ስለነፃነቱ መክሯል፤ የትግል መሪዎቹንም መርጧል፡፡ በጉባኤው ላይ የአርማጭሆ ህዝብም ተገኝቶ በጋራ ጠላታቸው ላይ የተባበረ ክንዳቸውን ሊያሳርፉ ቃል ተገባብተዋል፡፡
የወልቃይት ህዝብ ለነፃነቱ ሊታገል ከመቸውም ጊዜ በላይ ቆርጦ በአንድነት መነሳቱ ታወቀ፡፡
====================================================
የወልቃይት ህዝብ ህወሓት ገና ከሽፍትነቱ ጀምሮ ተደጋጋሚ ግፍና በደል ያደረሰበት በመሆኑ መቸም የማይፈታ ቂም አለው፡፡ ህወሓት ስልጣን ላይ ከወጣ በኋላ ደግሞ ሳይፈልግ ከጎንደር እንዲገነጠል ተደርጎ ወደ ትግራይ ክልል በመጠቃለሉ ሲያነሳው የቆየው ያልተመለሰ ጥያቄ አለው፡፡
ህወሓት የወልቃይት ህዝብ ያነሳውን ጥያቄ መሰረት በማድረግ የጀመረውን የነፃነት ትግል እንቅስቃሴ ጦር ኃይሉን ተጠቅሞ ለመደፍጠጥ ወደ አካባቢው ያለማቋረጥ ሰራዊት እያዘመተ አሰቃቂ የህዝብ ጭፍጨፋ በማድረግ ዘር ማጥፋት ፈፅሟል፡፡...
ሆኖም ህወሓት የወልቃይትን ህዝብ በጥይት በመግደል ዝም ማሰኘት ሳይችል ቀርቶ ዛሬ የበለጠ ተደራጅቶበት ጠብመንጃውን ወልውሎ በአንድነት ተነስቷል፡፡ ወደ በረሃ እየወረደ አርቨኞች ግንቦት 7 እያፋፋመው የሚገኘውን አርበኝነት የሚቀላቀለውም ከዕለት ዕለት ቁጥሩ በእጅጉ አይሏል፡፡
ከሰሞኑ ደግሞ የወልቃይት ሰው ማር ዘነብ ልዩ ቦታው ቴፍ ላይ በመሰባሰብ ስለነፃነቱ መክሯል፤ የትግል መሪዎቹንም መርጧል፡፡ በጉባኤው ላይ የአርማጭሆ ህዝብም ተገኝቶ በጋራ ጠላታቸው ላይ የተባበረ ክንዳቸውን ሊያሳርፉ ቃል ተገባብተዋል፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)