Saturday, 10 October 2015

LET'S STAND TOGETHER TO STOP VIOLENCE AGAINST WOMEN!!

«አሳዛኝ ዜና»
ይህቺ ፎቶዋን የምትመለከቱት ወጣት ማኅደር ጫኔ ትባላለች፡፡ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የህክምና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪ ስትሆን፣ ለእረፍት ተወልዳ ያደገችበት አጋሮ ከተማ ቆይታ ወደ ጎንደር ከተመለሰች 2 ሳምንት አልሞላም፡፡ ከትላንት ወዲያ (መስከረም 26፣ 2008 ዓ.ም.) ምሽት ላይ ጎንደር፣ ኤምባሲ ሆቴል አካባቢ ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሚኒባስ መኪና መጥተው በስለት ወግተዋት በመጡበት መኪና በማምለጣቸው ሕይወቷ አልፏል፡፡ ማኅደር መልካም ባህሪ ያላት ወጣት እንደሆነች የሚያውቃት ሰው ሁሉ ይመሰክራል፤ ለቤተሰቧ ብቸኛ ሴት ልጅ እንደመሆኗ በተለይ ከእናቷ ጋር ልዩ ፍቅር የነበራት ልጅ ነች፡፡ ለቤተሰቦቿ፣ ለጓደኞቿ እና ለሚያውቋት ሁሉ መጽናናትን እየተመኘን፣ ይህን ማስታወሻ “ሼር” በማድረግ ፍትሕ እንዲሰፍን የበኩላችንን እናበርክት፡፡
LET'S STAND TOGETHER TO STOP VIOLENCE AGAINST WOMEN!!
በንፁኃን ላይ የሚፈፀም የግፍ ግድያ ይቁም!!
ፋስት መረጃ ዶት ኮም / በእዮብ ሙላቱ
ለወዳጅ ዘመዶቿ እና ለቤተሰቦቿ መፅናናትን እንመኛለን።

No comments:

Post a Comment