አርበኞች ግንቦት ሰባት ገንዘባችንን ዘረፈው ( ሄኖክ የሺጥላ )
ትግሉ ገንዘብ ያስፈልገዋል ማለት ትግሉ በገንዘብ ነው የሚመጣው ማለት አይደለም። አርበኞች ግንቦት ሰባት እርዳታ ያስፈልጋቸዋል ማለት፣ ገንዘብ ስላዋጣሁ አንገረብን አልፋችሁ ካልሄዳችሁ ውርድ ከራሴ የሚያስብል አይመስለኝም ። ትግል በገንዘብ ይደገፍ ይሆናል እንጂ ፣ ገንዝብ የድል መሰረት ሆኖ ትግሉን ወደፊት አይገፋውም ። ትግሉ ብረት የተሸከሙት ሰዎች ቁርጠኝነት እና መለኮታዊ ዕድል ድምር ነው ። ገንዘብ ያንን ዕድል ማስፈጸሚያ እና አጋጣሚውን መፍጠሪያ ነው ።
ስለዚህ ትግሉ ባለ ድል የሚሆነው በናንተ ድጋፍ ነው ሲባል ፣ የቁስ ብቻ ሳይሆን የመንፈስ መሆኑን አትርሱ። በተጨማሪም ፣ ገንዘብ ስለረዳችሁ ብቻ አርበኞች ግንቦት ሰባት ህወሃትን የማሸነፍ ግዴታ አትጣሉበት ። እናንተም ትግሉ ወደ ድል እንዲቀየር በሃሳብ እርዱ ። ገንዘብ ባለ ድል ቢያደርግ ኖሮ ታላቋ አማሪካ በሄደችበት ባሸነፈች ነበር ። የልጆቹን ወኔ ፣ የአላማ ጽናት እና የሕይወት መስዋትነት ፣ ከባህር ማዶ በጨረታ መሃል በምትረጩት ገንዘብ ልክ አትዩት ። እያደረጋችሁት ያለውን እኔ በበኩሌ አደንቃለሁ ። ግን መዋጮ የቁጣ እና የየት ደረሰ ሊቸንሳ አይመስለኝም ። ሰው ህይወቱን በሚያዋጣበት ትግል ፣ የገንዘብ እርዳታ አድርጎ ያንን እንደ ትልቅ አስተዋጾ መቁጠር የሚፈልግ ካለ ፣ ልክ አይመስለኝም ። እርዱ ፣ ግን ደሞ አትታበዩ ። የምናደርገው ነገር ሁሉ ለራሳችን ነውና !
ስለዚህ ትግሉ ባለ ድል የሚሆነው በናንተ ድጋፍ ነው ሲባል ፣ የቁስ ብቻ ሳይሆን የመንፈስ መሆኑን አትርሱ። በተጨማሪም ፣ ገንዘብ ስለረዳችሁ ብቻ አርበኞች ግንቦት ሰባት ህወሃትን የማሸነፍ ግዴታ አትጣሉበት ። እናንተም ትግሉ ወደ ድል እንዲቀየር በሃሳብ እርዱ ። ገንዘብ ባለ ድል ቢያደርግ ኖሮ ታላቋ አማሪካ በሄደችበት ባሸነፈች ነበር ። የልጆቹን ወኔ ፣ የአላማ ጽናት እና የሕይወት መስዋትነት ፣ ከባህር ማዶ በጨረታ መሃል በምትረጩት ገንዘብ ልክ አትዩት ። እያደረጋችሁት ያለውን እኔ በበኩሌ አደንቃለሁ ። ግን መዋጮ የቁጣ እና የየት ደረሰ ሊቸንሳ አይመስለኝም ። ሰው ህይወቱን በሚያዋጣበት ትግል ፣ የገንዘብ እርዳታ አድርጎ ያንን እንደ ትልቅ አስተዋጾ መቁጠር የሚፈልግ ካለ ፣ ልክ አይመስለኝም ። እርዱ ፣ ግን ደሞ አትታበዩ ። የምናደርገው ነገር ሁሉ ለራሳችን ነውና !
No comments:
Post a Comment