Wednesday, 17 June 2015

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ አሁንም ስቃይ ላይ ናቸው

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ አሁንም ስቃይ ላይ ናቸው ።_"በህይወት የመቆየት ምክንያት የለኝም። መሞት እፈልጋለሁ" አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ከህወሀት የማሰቃያ ጨለማ ቤት። ዛሬ የእንግሊዙ ጋዜጣ ዘ ኢንድፔንደንት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የጤንነት ሁኔታ በጣም አስጊ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ዘገቧል። አቶ አንዳርጋቸው ፍጹም ጤናቸው መታወኩና ከበፊቱ ምንም አይነት ለውጥ አለማሳየቱ ስቃዩም የጨመረ መሆኑን ። ለባሌቤታቸው ከእንግሊዝ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የተሰጣቸው ሪፖርት አስደንጋጭ እንደሆነ ጋዜጣው ጠቅሷል።
ባለፈው አንድ ኣመት በማይታወቅ ምስጢራዊ እስር ቤት ታስሮ የሚገኘው የነጻነት ኣርበኛው የኣንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ኣሳሳቢ መሆኑን እና ያለበትን ሁኔታ አስመልክቶ ፍራቻዎች እየሰፉ መምጣታቸውን የተገለጸ ሲሆን የብሪጣንያ መንግስት ታጋዩን አንዲያስለቅቅ ግፊት አየተደረገበት አንደሆነና የኣንዳርጋቸው ጉዳይ ኣሳሳቢ በመሆኑ የተባበሩት መንግስታት የቶርቸር ጉዳዮችን የሚመለከተው ክፍል ሃላፊ የሆኑት ጆን ማንዴዝ ጉዳዩን ማየት የጀመሩ ሲሆን ታጋይ ኣንዳርጋቸው ተለቆ ወደ አንግሊዝ አንዲመለስ ኣስፈላጊ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠላቸው ታውቍል።

No comments:

Post a Comment